Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Salini Costruttori says only about 100 people died. Who then, murdered the 15K people which OPDO confirmed to have died?

Post by Za-Ilmaknun » 05 Sep 2025, 13:19

በሕዳሴ ግድብ ግንባታ "15 ሺህ ሰዎች ሞተዋል" ስለመባሉ የግድቡ የሠራተኞች ደኅንነት ባለሙያዎች ምን ይላሉ?

ቢቢሲ ያነጋገራቸው፤ የቀድሞው "ሳሊኒ ኢምፕሬጂሎ" የደኅንነት አስተባባሪ እና መሃንዲስ ከግንባታ ሥራ ጋር በተያያዘ ይህንን ያህል ሰው ሞቷል መባሉን ውድቅ አድርገዋል።

"ዊ ቢውልድ" በሚል ስያሜውን የቀየረው ይህ የሕዳሴ ግድብ ዋና ተቋራጭ፤ በግንባታው ሂደት የሲቪል ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል።

የተቋራጩ የ"ኸልዝ ኤንድ ሴፍቲ ኢንቫይሮመንት" መሃንዲስ የሆኑት ኢንጂነር ሞገስ የሺዋስ ከመጋቢት 2004 ዓ.ም. እስከ ባለፈው ግንቦት 2017 ዓ.ም. ድረስ በግንባታው ላይ ሰርተዋል።

"ኸልዝ ኤንድ ሴፍቲ ኢንቫይሮመንት" ክፍል አስተባባሪ የነበሩት ሌላኛው ባለሙያ ምንተስኖት አየለ በበኩላቸው ከ2004 ዓ.ም. አንስቶ ለአስር ዓመታት ገደማ ግንባታው ላይ ቆይተዋል።

አብዛኛውን የሰው ኃይል የሚያሰማራው "ዊ ቢውልድ" ሠራተኞችን የሥራ ላይ ደኅንነት የመከታተል እና የመመዝገብ ኃላፊነት ያላቸው እነዚህ ባለሙያዎች፤ በግንባታው ሂደት ውስጥ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች መኖራቸውን ያስረዳሉ።

እስከ 2014 ዓ.ም. ድረስ ኸልዝ ኤንድ ሴፍቲ ኢንቫይሮመንት ኮርዲኔተር ሆነው የሠሩት ምንተስኖት "በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎች የሞቱበት መንገድ አለ" ይላሉ።

"ከሥራ ጋር በተገናኘ በአደጋ የሚሞቱበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል። የግድቡን ኅልውና በማስጠበቅ፣ ከተለያዩ ቦታዎች ላይ ቁሳቁሶችን በማመላለስ፣ ጥቃት ሲደርስ ስለነበር በዚያ ሰዓት የተሰዉ ወገኖችም፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላትም ሊኖሩ ይችላሉ" ብለዋል።

ነገር ግን በትክክል መናገር የሚችሉት ከግድቡ ግንባታ ሥራ ጋር በተያያዘ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን በተመለከተ እንደሆነ አስረድተዋል። "ከዚህ ጋር በተያያዘ የነበረው ሞት በጣም ጥቂት ነው። 15 ሺህ ከሚለው አንጻር ጋር ሲታይ በጣም ጥቂት ነው የነበረው" ብለዋል።

"እኛ ሳሊኒ ጋር የነበረው ከሥራ ጋር የተያያዘ የሞተ ሰው ከ100 የሚያልፍ አይመስለኝም። 100ም የሚደርስ አይመስለኝም" ሲሉም አክለዋል።

እስከ ግንቦት ድረስ የኮንትራክተሩ የኸልዝ ኤንድ ሴፍቲ ኢንቫይሮመንት ኢንጂነር የነበሩት ሞገስም በዚህ ሃሳብ ይስማማሉ።

ኢንጂነሩ፤ "ሥራውም ይመለከተኝ ስለነበር፤ እንመዘገበውም ስለነበረ ዳታው [መረጃ] ነበረኝ። ባለኝ ዳታ መሠረት እስከ ነበርኩበት ጊዜ ድረስ እኔ የማውቀው ቁጥር [የሞቱ ሠራተኞች ብዛት] 25 አካባቢ ነው፤ ድርጅቱ የሚያውቀውም ይህንን ነው" በማለት የሞቱ ሠራተኞች ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c2dngye9rzzo

Meleket
Member
Posts: 4776
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Salini Costruttori says only about 100 people died. Who then, murdered the 15K people which OPDO confirmed to have d

Post by Meleket » 06 Sep 2025, 02:32

ነፍስኄር ኢንጅነር ስመኘው በቀለ የ14ሺ ሰዉ ግምት መሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ተገልጿል ማለት ነው?!

Post Reply