ኢትዮጵያ ውስጥ "አጥፍተው የሚጠፉ ድሮኖች በከፍተኛ ቁጥር እየተመረቱ" መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ
ዐቢይ፤ በተቋሙ ያደረጉትን ጉብኝት በተመለከተ በሰጡት ገለጻ፤ "የምናመርታቸው [ድሮኖች] በውስን ቦታ የታጠሩ ሳይሆን፤ ለኮሜርሻል [ንግድ] ዓላማ የሚውሉ፣ ለሰርቬላንስ [ቅኝት] ዓላማ የሚውሉ፣ ለኦፕሬሽን [ለወታደራዊ ተልዕኮ] ዓላማ የሚውሉ በጣም በርካታ ድሮኖችን እያመረትን ነው" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአንድ ሀገር "አጠቃላይ ኢኮኖሚ ጉዞ መስመር እየያዘ ሲሄድ" በቀጣይነት መታሰብ የሚገባው የወታደራዊ አቅም ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል።
በኢኮኖሚው ዘርፍ የተጀመሩ ጉዞዎችን "በወታደራዊ አቅም እያስደገፉ መሄድ" እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።
"በእርሻ ያመጣነው ውጤት፣ በማዕድን ያመጣነው ውጤት፣ በእንደዚህ ያለ አቅም ካልተደገፈ፤ ብዙ ባንዳ እና ባዳ ባለበት ከባቢ ላይ አቅም ወሳኝ ነው። አቅም ከሌለ ማስጠበቅ ያስቸግራል" ሲሉም ተደምጠዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy850nwwjxwo
The embassy is endorsing this "miraculous transformation" of the economy and the leadership role of the "governor'. It speaks volumes why the U.S is silent about the bloodletting in the country. They are lending money to a country which prioritizes the production of mass murdering machinery while millions are going to bed empty belly every night.