በዩናይትድ ኪንግደም ቁጣ እና ተቃውሞ የቀሰቀሰው የኢትዮጵያዊው ስደተኛ ክስ
ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ከገባ በኋላ በቀናት ውስጥ በታዳጊ ሴቶች ላይ ወሲባዊ ትንኮሳ ፈጽሟል በሚል ባለፈው ሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ የተከሰሰው ኢትዮጵያዊ ጉዳይ በአገሬው ዜጎች ዘንድ ቁጣ እና ተቃውሞን ቀስቅሷል።
ሀዱሽ ገብረሥላሴ ቅባቱ የተባለው ግለሰብ ኤሲክስ በተባለችው ከተማ ውስጥ ከሚኖርበት የስደተኞች መጠለያ ሆቴል አቅራቢያ በሁለት ቀናት ውስጥ ፈጸመው ተብሎ የተጠረጠረበት የወሲባዊ ጥቃት ክስ በፍርድ ቤት እየታየ ነው።
ነገር ግን ይህ ክስተት በነዋሪዎች ዘንድ ስጋትን ፈጥሮ ላለፉት ሁለት ወራት ጥገኝነት ጠያቂዎች ያረፉበት ሆቴል እንዲዘጋ እና ስደተኞቹ ከከተማዋ እንዲወጡ የሚጠይቁ የተቃውሞ ሰልፎች አካሂደዋል።
ተመሳሳይ ስጋትም በሌሎች አካባቢዎች እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።
ትናንት ማክሰኞ በድጋሚ ፍርድ ቤት የቀረበው ሀዱሽ ድርጊቱን አለመፈጸሙን ገልጾ ቢከራከርም፣ ሁለት የ14 ዓመት ልጆችን በከተማዋ ማዕከላዊ ክፍል ውስጥ ባገኘበት ጊዜ "ከእነሱ ልጅ መውለድ እንደሚፈልግ" እና ሊስማቸው ሞክሯል የሚል ክስ ለፍርድ ቤቱ ቀርቧል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx29jdrq7x7o
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40