Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11381
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Abiy Ahmed's Legacy

Post by sarcasm » 15 Aug 2025, 07:31

ዛሬ የአብይ ልደቱ ነው .... ልደቱን አስመልክቶ በእነዚህ ስራዎቹ እንዘክረዋለን ...

* ከአንድ ሚሊዮን ሰው በላይ ያለ*ቀበ*ት ጦርነት አዋልዷል

* በእሱ ዘመን ከሃያ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከአካባቢው ተፈናቅሏል

* የሰው ህይወት ከችግኝና ከዘንባባ የረከሰበት ስርዓት ፈጥሯል

* የጎረቤት ሀገር ሰራዊት አስገብቶ የገዛ ዜጎቹን አስ*ገድ*ሏል ፣ አስ*ደፍ*ሯል ፣ አፈ*ናቅ*ሏል

* በዘመነ አብይ የሰው ልጅ ከነ ህይወቱ ሲቃ*ጠል ፣ አህያ ላይ አስከሬን ተጭ*ኖ ሲፎከር ፣ አን*ገት በ*ቢላ ሲታ*ረድ አይተናል

* ህገመንግስት የተጣሰበት ፣ ክልሎች እርስ በርስ የሚዋጉበት ፣ በመንግሥት የሚታቀድ ቀውስ የሚጠነሰስበት ሀገር አዋልዷል

* ከ86 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከድህንት ወለል በታች በቀን አንድ ጊዜ መብላት እንዳይችልም ሆኗል

* በሀገራችን ሰላም ጠፍቷል ... ጦርነት በርትቷል

* የህግ የበላይነት ተጠያቂነት የሚባሉ ነገሮች ቀርተዋል

* ፍትህ የለም ... ማንም ያሻውን የሚያደርግባት ሀገር ሆናለች

* የሀገሪቱን ሀብት በቅንጡ ፓርክና ቤተመንግሥት ላይ አባክኗል

* ከድሃ ሃገር ካዝና ሪዞርቶችን እየገነባ ይመፃደቃል

* የኢትዮጵያ ብር እጅግ የተዳከመ እንዲሆን አድርጓል

* የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሉአላዊነት ለIMF ሸጧል

* ኢኮኖሚዋ የደቀቀ ፣ ህዝቦቿ በተስፋ መቁረጥ መሄጃ ያጡ እንዲሆን አድርጓል

* ኢትዮጵያን በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በየእለቱ የሚሰደዱባት ሀገር አድርጓታል

* መምህራን ፣ የህክምና ባለሞያዎች ፣ የመንግስት ሰራተኞች እየሰሩ እየፈጉ እንኳን ለእለት ጉርስ የሚሆን ምግብ አጥተዋል

* ኢንቨስትመንት ጠፍቷል የውጭ ባለሃብቶች ሸሽተዋል

* ነጋዴው በከፍተኛ ግብር እንዲጨልል ኪሳራ እንዲከነናብ ሆኗል

* በቀጠናው የተከበረችውን ሀገር ዋጋ ቢስ አድርጓታል

* ከሁሉም ጎረቤት ሀገራት ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቷል

* የዲፕሎማሲ ክሽፈት ፈጥሯል ፣ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር አለመተማመን እንዲኖር አድርጓል

* ወዳጆችን የሚያርቅ የውጭ ፖሊሲ ተከትሏል

* ወጥቶ መግባት የማይቻልበት ፣ ሰርቶ መግባት አዳጋች የሆነበት የስጋት ምህዳር ፈጥሯል

* የትጥቅ ትግል በየአካባቢው እንዲቀጣጠል በር ከፍቷል

* ክልሎች እርስ በርስ እንዳይተማመኑ አድርጓል

በእርግጥ አብይ አህመድ

* ጥቂት ባለሃብቶች የሚዝናኑበት ሪዞርቶችና ፓርኮችን በከፍተኛ ገንዘብ ፈሰስ አድርጎ በመገንባት የኢትዮጵያ ገፅታ ይህ ነው ብሏል።

* ለሀገር የሚጠቅሙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ሳይገነባ ለብልጭልጭና ለመብራት ትኩረት ሰጥቷል።

* ብሔራዊ መግባባት እያለ ከእራስ ጋር የሚደረግ ምክክር እያካሄደ እራሳችንን እንሸውድ ብሏል ...

ሌላ የሰራው አንዳች ነገር የለውም ....
.
.
.
Please wait, video is loading...