Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member
Posts: 4627
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Meleket » 01 Jul 2025, 12:03

ክልል ትግራይ ወልቃይትን ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ያካትታል ስትሉ እንሰማለን። የነዚህ ኣካባቢ ሰዎች 90% ትግርኛ ተናጋሪ ናቸውም ስትሉ ይሰማል።

እስቲ ለጨዋታ ያህል ይህ ያላችሁት ትክክል ነው እንበል። በስሌታችሁ መሰረት የተቀረው 10% ኣማርኛ ወይ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ ተናጋሪ ሳይሆን ኣይቀርም ብለን እንገምታለን።

ትግራይ ክልል ውስጥ 3 ብሄረሰቦች እነሱም ትግሬ ኩናማና ኢሮብ ነው የሚገኙት ስትሉም ትደመጣላችሁ! የሕወሓት ማኒፌስቶ ሳይቀር እንዲያ ነው የሚለው ሲባልም እንሰማለን!

ታዲያ ወልቃይት ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ውስጥ ያሉት ከትግርኛ ውጭ ኣማርኛ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ የሚናገሩት ሰዎች ከኩናማ ትግሬና ኢሮብ ጋር ክልል ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ ለምንድን ነው የማትሉት? ለምንድን ነው ትግራይ ውስጥ 3 ብሄሮች ነው ያሉት የምትሉት? ከ3 በላይ ኣይሆኑም እንዴ? የሆነ የተዘባረቀ ነገርማ ኣለ!

ማብራሪያ እስቲ ከትግራይ ሊቃዉንት ይሰጥበት፡ መቼም ስለ ጐረቤቶቻችን ማወቅና መጠዬቅ ኣይቻልም ኣይባልም፡ ምክንያቱ ዘመኑ “ዘመነ-ጽምዶ” ነው እያላችሁ ስለሆነ፡ ጥያቂያችን ተገቢነት ያለው ይመስለናል። እዉነተኛ ጽምዶ፡ እዉነትን በመሸፋፈን እዉን ኣይሆንም። ገለጥለጥ አድርጋችሁ እስቲ ንገሩን! ያልገባንን እንዲገባንም ኣስረዱን! ለጨዋታ ያህል ነው!
:mrgreen:


Naga Tuma
Member+
Posts: 6230
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Naga Tuma » 01 Jul 2025, 16:12

Meleket wrote:
01 Jul 2025, 12:03
ለምንድን ነው ትግራይ ውስጥ 3 ብሄሮች ነው ያሉት የምትሉት? ከ3 በላይ ኣይሆኑም እንዴ? የሆነ የተዘባረቀ ነገርማ ኣለ!
የተዘባረቀ ነገር ቢኖር ነዉ እኮ ቤት ብሎ ቤተሰብ ከተባለ ሃገር ብሎ ብሔር እና እግዛብሔር ይባላል ማለት የማትችለዉ።

ቤት ብሎ ቤተሰብ ከተባለ ሃገር ብሎ ብሔር ይባላል ማለት ያልቻለ እንዴት ነዉ የመሃል እና የመስመር ዳኛ መሆን የቻለዉ?

ቤተሰብ ከመሃል እስከ ሃገር መስመር ነዉ እኮ።

እኛ በምናዉቀዉ ባህል ቤተሰብ ዉስጥ የተወለደ ልጅ ለአቅመ አዳም ከደረሰ ቀን ጀምሮ ቤተሰቡን ለማሻሻል፣ ለማበልጸግ፣ የቤተሰቡን ስም ከፍ ለማድረግ፣ ወዘተ ተግቶ መስራት የሚጠበቅበት መሆኑን ነዉ።

የተወልድክበት ቤተሰብ ዉስጥ የቤተሰቡ ልጅ መሆንህን እደራደራለሁ ብትል ሰዉን ታስቃለህ።
እዉነተኛ ጽምዶ፡ እዉነትን በመሸፋፈን እዉን ኣይሆንም። ገለጥለጥ አድርጋችሁ እስቲ ንገሩን! ያልገባንን እንዲገባንም ኣስረዱን! ለጨዋታ ያህል ነው!
ያልገባን እንዲገባን ነዉ እያልክ እንዴት ነዉ ለጫወታ ያህል ነዉ የምትለዉ?

ይህ በጀበና ዙርያ ቡና እየጠጡ የሚዝናኑበት ጫወታ ኣይዴለም።

ያልገባህን ሃምሳ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ለማስረዳት ተለፍቷል።

መቶ ሃያ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ለማስረዳት ተለፍቷል።

አምስት መቶ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ለማስረዳት ተለፍቷል።

ሁለት ሺህ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ለማስረዳት ተለፍቷል።

ኣሁንማ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ለማስረዳት እየተለፋ ነዉ።

ይህ ሁሉ ማስረዳት ግልጽ የምያደርገዉ ኣንድ ነገር ኣለ። የቤተሰብ በርጩማ ይነቃነቅ ሲባል የቤተሰቡ አባሎች ሁሉ ብቻ ሳይሆን ከቤተሰብ ዉጪ የሚኖሩ ብዙዎች የበርጩማዉ ረሃብተኞች የሚሆኑ መሆኑን ነዉ።

ለዚህ ነዉ ብልህ ቤተሰብ የቤተሰቡ በርጩማ ይነቃነቅ ከማለት በፊት ቢነቃነቅ ቀጣይነቱ እንዲህ ነዉ ብሎ ቀድሞ የሚዘጋጀዉ።

የሶስት ሺህ አምስት መቶ ዓመታት ገደማ ወደ ኋላ ተመልሶ ማስረዳት ሲገባደድ የኢትዮጵያ ፖለትካ የብሔር ፖለትካ ሳይሆን የጎሳዎች ቋንቋዎች ፖለትካ መሆኑ በጣም ግልጽ ሊሆን ይችላል።

ያ ለሁሉም ግልጽ ሲሆን በጀበና ዙርያ በበጩማዎች ላይ ተቀምጠዉ፣ እንደ ተከበሩት ንጉሶቹ፣ ፌደራሊዝም ለማለት ያልተኮላተፉት፣ በጎሳዎች ቋንቋዎች ቋንቋ ምን ማለት ነዉ? ቆንቆ ምን ማለት ነዉ? ሰበ ምን ማለት ነዉ? ሰብ ምን ማለት ነዉ? እያሉ ቆጥሬ መጨረስ የማልችለዉን መቁጠር ይችላሉ።

አሊ ብራ ራሱ ቢነሳ ቆጥሮ መጨረስ የሚችል ኣይመስለኝም። ምናልባት ብራን በሪኤ፣ ብርሃን ተኤ፣ ብራይት ጄዸሜ ብሎ የምያዝናናን በሰብኛ ያቀነቅን ይሆናል።

ያ ሲሆን አክሱም እና አምቦ ከተማዎች ዉስጥ ኖሮ የሁለቱንም ከተማዎች የጀበና ዙርያ ጫወታዎችን ተመሳሳይነት የወደደዉ እና ያደነቀዉ ሰዉ ዐይነት የኣንድ ቤተሰብ ዐይነት ጫወታ፣ የኣንድ ብሔር ጫወታ ሊሆን ይችል ይሆናል።

Meleket
Member
Posts: 4627
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Meleket » 02 Jul 2025, 04:07

ወዳጃችን ኣዅሱመጫላ ማንቝርትህን ያዝንህ መሰል። ለተጠየቅከው ጥያቄ ሁነኛ መልስ ኣጣህ እንዴ? እስቲ ገብሩ ዓዴት ወይም ሰብ ዝሰአነ ሰብ ወይም ሃይለ ደደቢት ወይም ስታሊን ወይም ጎደፋይ ወይም ዶሪ ወይም ጌቾ ወይም ደብሪጽ ወዘተንም ቢሆን ጠይቀህ መልስ ኣጋራን። ይህ በ 1994 በኢሕኣዲግ ግዜ የተካሄደ የህዝብ ቆጠራ ውጤት እንደሚያመለክተው
ትግራይ ውስጥ በ % ሲገለጽ ነዋሪው ይህን ይመስላል https://www.ethiopia-insight.com/2022/0 ... '%20favor.
94.75% ትግርኛ
2.59% ኣማርኛ :mrgreen:
0.73% ሳሆ(ኢሮብ መሆኑ ነው)
0.49% አገው :mrgreen:
0.24% ኣፋር :mrgreen:
0.12% ኦሮሞ :mrgreen:
0.06% ኩናማ
0.02% አርጎባ
0.92% ኤርትራዉያን
0.08%% ወዘተ ይኖራሉ ተብሏል።
በምን ሂሳብ ነው ታዲያ የትግራይ ኣንቂዎች እነ ብርሃነ ገብረገርግስ (ዋጣ) እንዲሁም የኛው ዓወል ሰዒድ፡ ትግራይ ውስጥ 3 ብሄረሰቦች ነው ያሉት እነሱም ትግሬ፡ ኩናማና ኢሮብ(ሳሆ) የሚሉን፡ ከኩናማዎችና ከኢሮብ (ሳሆዎች) የበዙትን ኣማራዎችን፡ ኣገዎችን ኣፋሮችንና ኦሮሞዎችንም ጭምር የት ትተዋቸው ነው? :mrgreen:


The 1994 Population and Housing Census of Ethiopia: Tigray Region VII [p. 37]


ጭራሽ ይህ ድረገጽ https://en.wikipedia.org/wiki/Welkait ወልቃይት ላይ የ2007 ቆጠራ
93.52% ትግርኛ
6.48% ኣማርኛ :mrgreen:
ወዘተ ይኖራሉ ተብሏል። ታዲያ ትግራይ ውስጥ 4ተኛ ብሄር ተብሎ ኣማራ መመዝገብ ይገባዋል ወይስ አይገባዉም! ተመካክራችሁም ቢሆን መልስ ኣምጡ፡ ካልሆነ ትዝብት ውስጥ ኣስገብተናችኋል እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር!

የኤርትራና የኢትዮጵያ ደንበር ጉዳይማ ሄግ ጨርሶታል እኮ፡ ዘለቄታዊ ሰላም ይገኝ ዘንድ ደግሞ ችካል ተቸክሎ መካለሉ የግዜ ጉዳይ እንጂ ኣይቀሬ ነው! viewtopic.php?f=2&t=308857
:mrgreen:
Axumezana wrote:
01 Jul 2025, 14:20
ድንበር ይካለል!
Naga Tuma wrote:
01 Jul 2025, 16:12
...

Meleket
Member
Posts: 4627
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Meleket » 02 Jul 2025, 11:09

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ ኣስተዳዳሪዎች ወዲ ወረደ ሆነ ምክትሉ ኣይተ ኣማኑኤል ኣሰፋም ለዚህ ጥያቄ መልሳቸው ምን ይሆን? ሰምቶ ያልሰማ መምሰል መቼም ምላሽ ሊሆን ኣይችልም፡ በብዙዎች ትዝብት ውስጥ ከመግባት ኣያድንም።

Wedi
Member+
Posts: 8486
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Wedi » 02 Jul 2025, 12:34

Meleket wrote:
01 Jul 2025, 12:03
ክልል ትግራይ ወልቃይትን ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ያካትታል ስትሉ እንሰማለን። የነዚህ ኣካባቢ ሰዎች 90% ትግርኛ ተናጋሪ ናቸውም ስትሉ ይሰማል።

እስቲ ለጨዋታ ያህል ይህ ያላችሁት ትክክል ነው እንበል። በስሌታችሁ መሰረት የተቀረው 10% ኣማርኛ ወይ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ ተናጋሪ ሳይሆን ኣይቀርም ብለን እንገምታለን።

ትግራይ ክልል ውስጥ 3 ብሄረሰቦች እነሱም ትግሬ ኩናማና ኢሮብ ነው የሚገኙት ስትሉም ትደመጣላችሁ! የሕወሓት ማኒፌስቶ ሳይቀር እንዲያ ነው የሚለው ሲባልም እንሰማለን!

ታዲያ ወልቃይት ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ውስጥ ያሉት ከትግርኛ ውጭ ኣማርኛ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ የሚናገሩት ሰዎች ከኩናማ ትግሬና ኢሮብ ጋር ክልል ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ ለምንድን ነው የማትሉት? ለምንድን ነው ትግራይ ውስጥ 3 ብሄሮች ነው ያሉት የምትሉት? ከ3 በላይ ኣይሆኑም እንዴ? የሆነ የተዘባረቀ ነገርማ ኣለ!

ማብራሪያ እስቲ ከትግራይ ሊቃዉንት ይሰጥበት፡ መቼም ስለ ጐረቤቶቻችን ማወቅና መጠዬቅ ኣይቻልም ኣይባልም፡ ምክንያቱ ዘመኑ “ዘመነ-ጽምዶ” ነው እያላችሁ ስለሆነ፡ ጥያቂያችን ተገቢነት ያለው ይመስለናል። እዉነተኛ ጽምዶ፡ እዉነትን በመሸፋፈን እዉን ኣይሆንም። ገለጥለጥ አድርጋችሁ እስቲ ንገሩን! ያልገባንን እንዲገባንም ኣስረዱን! ለጨዋታ ያህል ነው!
:mrgreen:

Naga Tuma
Member+
Posts: 6230
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Naga Tuma » 02 Jul 2025, 13:59

Meleket wrote:
01 Jul 2025, 12:03
… ትግራይ ውስጥ 3 ብሄሮች …
Meleket wrote:
01 Jul 2025, 12:03
…ትግራይ ውስጥ 3 ብሄረሰቦች …
ጥያቄዬ በከፊሉ ተመልሷል።

ቤት ብሎ ቤተሰብ ከተባለ ሃገር ብሎ ብሔር ይባላል ማለት ይቻላል።

ትለንት ኣስቤ የዘነጋሁኝ መሠረታዊ ጥያቄዉ ለምንድነዉ እንደ እኛ ኤርትራዊያን ሃደ ሕዝቢ፣ ሃደ ልቢ የማትሉት መሆን ነበረበት።

Meleket
Member
Posts: 4627
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ወጣሪና ኮርኳሪ ጥያቄ በተለይ ለትግራይ ሊቃዉንት!

Post by Meleket » 03 Jul 2025, 05:15

ወዳጃችን Wedi ፋኖ ከትግራይ ሃይሎች ጋር የሚኖረው ትስስር፡ የትግራይ ሃይሎች ለዚህች ጥያቄ በሚሰጡት መልስ ይመዘን ይሆናል ብለን እንገምታለን! የትግራይ ህዝብና የኣማራ ህዝብም እንደ ጥንቱ ያለ ኣንዳች ፍራቻ በሰላምና በፍቅር በመተማመንና በመተባበር ይበልጥ ይተሳሰሩ ዘንድ ጠባብም ትሁን እውነተኛዋን ጐደና መከተል የግድ ይላል። የትግራይ ፖለቲከኞች የአማራ ህዝብን እንደ ብሄርም ጭምር በትግራይ ክልል ውስጥ መገኘቱን በይፋ ማመን ይጠበቅባቸዋል። የህዝብ ቆጠራው ውጤት የሚመሰክረው ሓቅም ኣማሮች ከኩናሞችና ከኢሮቦች በላይ በብዛት ትግራይ ክልል ውስጥ እንደሚገኙ ነው! ቢባል ማን ነው ይህን ሊያስተባብል የሚችል፡ ተራ ካድሬ ካልሆነ በስተቀር።

ለማንኛውም በኤርትራና በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል ለሰላም የሚደረገውን ትጋት ስናበረታታ፡ በተመሳሳይ መልኩ በትግራይና በኣማራ ህዝብ እንዲሁም በሌሎች ህዝቦች መካከል የሚደረገው ትብብር ይጎመራ ዘንድ መልካም ምኞታችንን እንገልጣለን፡ እኛ ኤርትራዉያን የመሃልንናየመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር!

ሓሳብ ጽምዶ ኣብ ዞባና ንኪስስን፡ ጽምዶ ሕዝቢ ትግራይን ሕዝቢ ኣምሓራን እዉን ንኪዕወት፡ እዚኣ ቀላል ግን ድማ ግልጽቲ ሕቶ ብወገን ግዚያዊ መንግሥቲ ትግራይ ዀነ ብወገን ሕወሓትን ካልኦት ፓርቲታት ትግራይን ቕኑዕ ምላሽ ኪወሃባ ይግባእ። እቲ ምንታይ እንተተባህለ፡ ጽምዶ መሰረቱ ሓቂ ኪኸውን ስለዚግባእ፤ ሓቂ ዚደፈነን ዝዓበጠን ጽምዶ ፍረ ኣልቦ ስለዚኸውን።

Wedi wrote:
02 Jul 2025, 12:34
Meleket wrote:
01 Jul 2025, 12:03
ክልል ትግራይ ወልቃይትን ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ያካትታል ስትሉ እንሰማለን። የነዚህ ኣካባቢ ሰዎች 90% ትግርኛ ተናጋሪ ናቸውም ስትሉ ይሰማል።

እስቲ ለጨዋታ ያህል ይህ ያላችሁት ትክክል ነው እንበል። በስሌታችሁ መሰረት የተቀረው 10% ኣማርኛ ወይ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ ተናጋሪ ሳይሆን ኣይቀርም ብለን እንገምታለን።

ትግራይ ክልል ውስጥ 3 ብሄረሰቦች እነሱም ትግሬ ኩናማና ኢሮብ ነው የሚገኙት ስትሉም ትደመጣላችሁ! የሕወሓት ማኒፌስቶ ሳይቀር እንዲያ ነው የሚለው ሲባልም እንሰማለን!

ታዲያ ወልቃይት ጠ(ጸ)ገዴና ጠ(ጸ)ለምት ውስጥ ያሉት ከትግርኛ ውጭ ኣማርኛ ኣገውኛ ወይ ቅማንትኛ የሚናገሩት ሰዎች ከኩናማ ትግሬና ኢሮብ ጋር ክልል ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ ለምንድን ነው የማትሉት? ለምንድን ነው ትግራይ ውስጥ 3 ብሄሮች ነው ያሉት የምትሉት? ከ3 በላይ ኣይሆኑም እንዴ? የሆነ የተዘባረቀ ነገርማ ኣለ!

ማብራሪያ እስቲ ከትግራይ ሊቃዉንት ይሰጥበት፡ መቼም ስለ ጐረቤቶቻችን ማወቅና መጠዬቅ ኣይቻልም ኣይባልም፡ ምክንያቱ ዘመኑ “ዘመነ-ጽምዶ” ነው እያላችሁ ስለሆነ፡ ጥያቂያችን ተገቢነት ያለው ይመስለናል። እዉነተኛ ጽምዶ፡ እዉነትን በመሸፋፈን እዉን ኣይሆንም። ገለጥለጥ አድርጋችሁ እስቲ ንገሩን! ያልገባንን እንዲገባንም ኣስረዱን! ለጨዋታ ያህል ነው!
:mrgreen:

Post Reply