Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 36163
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የአቢይ አህመድ ወረራ በጉራጌ

Post by Horus » 29 Dec 2023, 04:03

ይህን ፖስት የምለጥፈው ስለ ኦሮሞ ወረራ ለማለቃቀስ አይደለም፤ እኛ ከ16ኛው ዘመን ጀምረን የምናውቀውና ኦሮሞ ጉራጌን ማጥፋት እንደ ማይችል ሺ ግዜ ስላረጋገጥን አንድ አስገራሚ ነገር ብቻ ልነግራችሁ ነው ።

ትላንት በሶዶ ቡታጀራ ሆሳዕና መንገድ (ጉራጌዎች በራሳቸው ገንዘብ ያሰሩት መንገድ፣ ገና የሜጫና ቱለማ መረዳጃ ማህበር ከኛ ኮርጀው ሳያቋቁሙ) 18 ንጹሃን መንገደኛ ጉራጌዎች በግፍ ተገደሉ ። ከዚያ አንድና ሁለት ቀን በፊት መርካቶ፣ አሜሪካን ግቢ፣ ጎጃም በረንዳ በሺዎች የሚቆጠሩ ጉራጌዎች ታፍሰው ታሰሩ ። ይህ ሁሉ እየሆነ እያለ ጉራጌው የምክር ቤት አባል ታረቀኝ ደግፌ የመከሰስ መብቱ በፓርላማው ተገፎ በወንጀል ሊያስሩት ወይም ሊገድሉት እየተሯሯጡ ናችው።

አሁን እነዚህን 3 ክስተቶች አያይዛችሁ ተመልከቱ ። በአንድ ቀጭን ያቢይ አህመድ ትዛዝ የተፈጸሙ ወንጀሎች ናችው ። አቢይ አህመድ ስልክ አንስቶ ያን ታረቀኝን መብቱን አንስተህ ቃሊቲ ክተትልኝ ይላል ። ይህን የሚያዘው ለዚያ እበት የፓርላማው ሊቀ መንበር ነው ። ቀጥሎ ስልክ ያነሳና የፖሊስ አዛዡን መርካቶ ሄደህ አንድ ሺ ጉራጌዎችን ከየሱቁ ልቀምልኝ፣ ያኔ በፍርሃት ይቀዝናሉ! ይለዋል ። በመጨረሻም በሸኔ ስም በምስጢር ያደራጃቸው የኦሮሙማ ኢምፓየር እርሾ ጦር ይደውልና እዚያ ጉራጌ መንገድ አስቁመህ መኪናችውን አቃጥለው በቂ ቁጥር ግደልልኝ ። በቂ ፍርሃት በውስጣቸው እንዲንቀጠቀጥ .... ይህ ነው የሆነው!

ሶስቱንም ነገሮች በአንድ ግዜ ያደረገው አቢይ አህመድ ነው ! ይህን መሰል የጂል እብሪት ግን ለጉራጌ ወጣት እጅግ ግዙፍ ማንቂያ ደወል ሆኖዋል! ጉራጌን እየወረረ ያለው አቢይ/ሺመልስ እንጂ ሸኔ አይደለም! ይህ ወሳኝ ግንዛቤ ነው ። ለዚህ ደሞ የጉራጌ ምላሽ የሚሆነው ኦሮሙማን ከ4 ኪሎ ማስወገድ ብቻ ነው


Post Reply