Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Zmeselo
- Senior Member+
- Posts: 34392
- Joined: 30 Jul 2010, 20:43
Post
by Zmeselo » 12 Mar 2025, 08:27
አላስፈላጊ ውሸቶች
አብይን ካወኩት ጊዜ ጀምሮ አንድ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር አላስፈላጊ ውሸት የሚዋሸው ነው። ለምሳሌ ያህል፣ ሰሞኑን ስለ ሆመቾ ጥይት ፋብሪካ የተናገረው ከአላስፈላጊ ውሸቶች ውስጥ አንዱ ማሳያ ነው። ስራ ከጀመረ ግምሽ ምዕተ-አመት የተጠጋውን ፋብሪካ እሱ እንዳቋቋመው አስመስሎ ሲናገር ነበር። ሆመቾ ለአመታት ከቀላል እስከ ከባድ መሳሪያን እንዲሁም ተተኩሾችን ሲያመርት እንዳልነበር፣ ‘ጥይት የማምረት ሙከራ’ ብቻ እንደነበር ተነገረ። ተተኳሽ ለሌሎች ሀገራት መሸጥም ገና አሁን እሱ ያስጀመረው እንደሆነ ዋሸ። እትዮጵያ ቢያንስ በ 2010 (እኤአ) ለሶማሊላንድ እና ደቡብ ሱዳን ተተኳሽ ትሸጥ እንደነበር በትግሉ ወቅት አንድ የመንግስት ኮምፒውተር ህክ ተደርጎ ካየሁት ዶክመንቶች ውስጥ ማየቴን አስታውሳለሁ።
የሚገርመው አብይ ይህን ሁሉ መዋሸት አያስፈልገውም ነበር። ፋብሪካውን በማዘመን እና ስራውን በማቀላጠፍ የሚያመርተውን ተተኳሽ ጥራት እና ብዛት ማሳደግ ሊጨበጨብለት የሚገባ ስራ ስለሆነ አብይ ይህንኑ ሃቅ ቢናገር ኖሮ ትዝብት ውስጥ ሳይገባ የሚፈልገውን የፖሊቲካ ትርፍ ማካበት ያስችለው ነበር። ፊልድ ማርሻሉ እኮ በዚያው ቦታና ጊዜ የተሰራው የማደስ እና የማዘመን ስራ እንደሆነ ሲገልጽ ነበር! በሆመቾ አዲስ የተሰራ ስራ ካለ ዋናው ግቢውን ማስዋብ ነው።
ድሮን ሰርተን ለራሳችን በቅተን ውጭ ለመላክ እየተዘጋጀን ነው ያለውም ሌላው አላስፈላጊ ውሸት ነው። የሆነው ድሮን መስራት ሳይሆን ‘መገጣጠም’ ( assembly) ነው። የድሮን ግብዓቶች (body, avionics, motors, software, remote control system etc) ውጪ ሀገር ተመርተው ከገቡ በኋላ ሀገር ውስጥ ተገጣጠሙ። ይሄም እራሱ በተሳከ መልኩ ከተሰራ የተወሰነ ወጪ የሚቀንስ ስለሆነ የሚናቅ ስልላልሆነ፣ ‘ድሮን መስራት ቻልን’ ብሎ ከመዋሸት ይልቅ ሃቁን ቢናገር በቂ ነበር።
ለምሳሌ ሀይሌ ገብረስላሴ ከ Hyundai Motor Company የመኪና አካላትን በማስገባት ኢትዮጲያ ውስጥ ይገጣጥማል። ይህ በራሱ ትልቅ አቅም ነው። ለሀግር ኢኮኖሚ ያለው አስተዋጾም ከፍተኛ ነው። ነገር ግን ሃይሌ ‘አዲስ መኪና ሰራሁ’ ቢል ያምርበታል? ከኩባንያው የህዝብ ግንኙነት ስራስ ይጥቅመዋል ወይስ ትዝብት ውስጥ ከቶ ስራውን ያራክሰዋል?
(በነገረችን ላይ የኢትዮጲያ አየር ሀይል የድሮን ፕሮጀክት የጀመረው አብይ እንደሚለው እሱ ስልጣን ከያዘ ወዲህ ሳይሆን ቀደም ብሎ ነበር። ደጀን አቪዬሽን በሚባል ድርጅት ስር በ2011 የሙከራ ስራ እንደተጀመረ የታወቀ ሃቅ ነው።)
በፖሊቲካ ውስጥ ከአንድ ጉዳይ ልገኝ የሚችለውን ትርፍ ከፍ ለማድረግ ዘገባውን ማጋነን እና ማጣፈጥ (spinning) የታወቀ ነው። ለዚህ ደግሞ ባለው እውነታ ላይ ትንሽ ውሽት ጣል ማድረግም የተለመደ ነው። ነገር ለማጋነነም ሆነ ለምጣፈጥ ውሸት ጣል የሚደረገው ለታሰበው የፖሊቲካ ትርፍ አስፈላጊ እና ጠቃሚ ከሆነ ነው። ለፕሮፓጋዳ የሚውል ማጋነን ወይም ውሸት ከመጠኑ ካለፈ፣ ከጠቅሙ ጉዳቱ ያመዘናንል። በወጥ ላይ የሚጨመር ወጥ ጋር ማመሳሰል ይቻላል። በመጠኑ ከተጨመረ ጣእሙን ሊጨምር ይችላል። ከልክ በላይ ከጨመርንበት ወጡን ከጥቅም ውጪ ያደርገዋል።
ነዳጅ ወደ ውጪ ለመላክ ዝግጁ ነን፣ ዝናብ በሰው ሰራሽ ዘዴ አዘነብን፣ በስንዴ ምርት እራሳችን ቻልን ወዘተ በአለፉት አመታት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰመናቸው ከጥቅማቸው ጉዳታቸው ያመዘነ አላስፈላጊ ውሸቶች ናቸው። ታዲያ አቢይ ለምን ሁሌም አላስፈላጊ ውሸት ይዋሻል? መልሱ ውሸት ሱስ/ በሽታ ስለሆነበት (pathological) ከመዋሸት እራሱን መቆጣጠር ስለማይችል ነው። የአንድ ሀገር መሪ አላስፈላጊና የማያቋርጥ ውሸት መደጋገም የሰውዬውን ታዓማኒነት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገረ መንግስትን ቅቡልነት ክፉኛ የሚሸረሽር ነው።
"Credibility is a leader's currency. With it, he or she is solvent; without it, he or she is bankrupt.” John Maxwell
-
Zmeselo
- Senior Member+
- Posts: 34392
- Joined: 30 Jul 2010, 20:43
Post
by Zmeselo » 12 Mar 2025, 08:47
They just lie, lie and lie!

-
Fed_Up
- Senior Member+
- Posts: 22384
- Joined: 15 Apr 2009, 10:50
Post
by Fed_Up » 12 Mar 2025, 12:27
Thank you Fiyameta. I was looking for this
Lying is the cultural game of Ethiopia‘s regime.

-
Fiyameta
- Senior Member
- Posts: 16192
- Joined: 02 Aug 2018, 22:59
Post
by Fiyameta » 12 Mar 2025, 13:02
I wouldn't be surprised if Ethiopia actually has less than 50 million people. They fabricated the "120 million" number to get more food-aid. Even the CIA called them ... A NATION OF LIARS & CHEATERS!
-
Fiyameta
- Senior Member
- Posts: 16192
- Joined: 02 Aug 2018, 22:59
Post
by Fiyameta » 12 Mar 2025, 14:12
There was no single census of any sort taken in Ethiopia since its creation in 1945. But there's been plenty of guesstimates as evidenced by the CIA report on Ethiopia.
If I have to guess, the country has a population of fewer than 50 million, of which 10 million are refugees scattered around the world. Real Talk!
-
union
- Senior Member
- Posts: 10469
- Joined: 14 Feb 2021, 15:24
Post
by union » 13 Mar 2025, 12:57
That is why we say it could be over 200 million people. We know Amara could be well over 100 million
Neve trust the CIA
