Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

በኦሮሚያ ክልል ሁለት ዞኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የዐይን እማኞች ተናገሩ

Post by Za-Ilmaknun » 01 Nov 2024, 18:57

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እና በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዱግዳ ወረዳ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎች መግደላቸውን እማኞች ተናገሩ። በወጫሌ ወረዳ ዛሬ ጠዋት ተፈጸመ በተባለው ጥቃት አቶ ንጉሴ ኮሩ የተባሉ አስተዳዳሪ ተገድለዋል። መቂ አካባቢ በተፈጸመ ሌላ ጥቃት እናቶች፣ አረጋውያን እና ሕጻናት መገደላቸውን፣ ቤቶች በእሳት መጋየታቸውን እማኞች አስረድተዋል።

በኦሮሚያ ክልልምስራቅ ሸዋ ዞን ዱግዳ ወረዳ ከመቂ ከተማ 18 ኪ.ሜ. ግድም ወጣ ብለው በሚገኙ ገጠራማ መንደሮች ተወስዷል በተባለው በዚህ የታጣቂዎች አስደንጋጭ ጥቃት በአከባቢው ባሉ ቤቶች ላይ እሳት በማያያዝ ብዙዎችን ደግሞ የጥይቀት እራት ስለመደረጉ ነው ተጎጂ የአይን እማኞች የገለጹት፡፡

እሮብ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት ተራዝሞ ነበር በተባለው በዚህ ጥቃት ሕጻናትን ጨምሮ እናቶችና አረጋውያን በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ተሰምቷል፡፡
ለደህንነታቸው ስባል ስማቸውን እንዳንጠቅስ ጠይቀው አስተያየታውን የሰጡን አንድ ተጎጂ እንዳሉትም በተለይም በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ ኤጄርሳ ሌሌ በሚባል ስፍራ የደረሰው ጉዳት እጅጉን አስከፊ ነው፡፡ “ጥቃቱ ያው እሮብ ምሽት ከሶስት ሰዓት ግድም ጀምሮ ነው ቤት በማቃጠል እና በግድያ የተጀመረው፡፡ ለዚህ ጥቃት ደግሞ “ሸነ የተባሉ ታጣቂዎች” ያቀረቡት ምክንያት ለምን ከመንግስት ጋር ተባበራችሁ የሚል ሲሆን ማህበረሰቡ ደግሞ ተደጋጋሚ ትቃት በታጣቂዎቹ ስደርስበት ስለነበር እራሱን በማደራጀት ለመከላከል በእንቅስቃሴ ላይ የነበረ ነው” ብለዋል፡፡
አስተያየት ሰጪው ተጎጂ አክለውም በአከባቢው ካሁን በፊት ተደጋጋሚየታጣቂዎች ጥቃት ስደርስበት የነበረ ቢሆን የአከባቢው ማህበረሰብ እንዲህ ያለ አስከፊ ጥቃትን አይቶት የማያውቅ ነው ብለዋል፡፡ “ከዚህ በፊትም ብዙ ሰው እያገቱ ለቀዋል፡፡ ብዙ ስቃይ ነው ስደርስ የነበረው፡፡ አሁን ከፋ ሆነና በዚች ምሽት በብዙ አቅጣጫ ገብተው ሰው ቤት እየዘጉ እሳት እያያዙበት ለመሮጥ የሞከረን ደግሞ በጥይት ስመቱ ነበር፡፡ በአንድ ጉድጓድ ሶስት-አራት ሰው እያደረግን ትናንት ወደ 40 ሰው ቀብረናል” ነው ያሉትም፡፡
https://www.dw.com/am/%E1%89%A0%E1%8A%A ... a-70664676