አንዷ ኢትዮጵያ በእነ ሆረስ ተብዬዉ የዚህ ፎረም ተካፋይ ግለሰብ አይነቶች ጭንቅላት ዉስጥ ያለች ኢትዮጵያ ናት። በብዙ ረገድ የምትዳሰስ አይደለችም፣ ከተዳሰሰችም በእንደዚህ ግለሰብ ጭንቅላት ዉስጥ ብቻ ናት፣ ከተጨባጭዋ ኢትዮጵያ ለየት ያለች ናት፣ በነሱ ጠባብ ጭንቅላት ዉስጥ ነዉ የተቀረፀችዉ፣ የራሱን ግላዊ መንፌስቶ ነደፍኩላት ብሎ በገቢያ ወጥቶ ይለፍፋል፣ ይመፀደቃል፣ ከእኔ በላይ ማንም የለም በማለት ይመፃደቃል።
በራሱ ጭንቅላት ዉስጥ ስለጠፈጠረች በራሱ ማን እንደምመረት፣ ማን እንደምጠብቃት ይወስንላታል። የወደ ፊት ጦር ኋይሏ ማን እንደሆነ በአደባባይ ወጥቶ መደብኩላት ብሎም ይመፃደቃል። ፋንዶ የምባል የሽብር ቡድን የወደፊት ወታደሮቿ ነዉ ብሎም ለመመፃደቅ ይደደዋል።
ከግማሽ በላይ የምሆኑ ሕዝቦቿ ለሱ ኢትዮጵያኖች አይደሉም፣ እኩል መብት ልኖራቸዉ አይገብም፣ ለመገዛት እንጂ ለመግዛት አልተፈጠሩም ብሎም ለማስተማር ይደደዋል። እነዚህ ከግማሽ በላይ የምሆኑት ሕዝቧ የከብቶች እረኞች እንጂ በፍፁም አገር ማስተዳደር አይችሉም፣ አይገባቸዉም ብሎም ለማስተማር ደፋ ቀና ይለናል። መንፌስቶ ተብዬዉ የግለሰብ ምንጭርጭር ፍላጎትም ይህንኑን አቋም ነዉ የምያንፀባርቀዉ።
ይህች ኢትዮጵያ የምትባል ዬት አከባቢ ነዉ የምትገኘዉ ስባል ደግሞ ያዉ የአፍሪካ ቀንድ አከባቢ መሆንዋን ነዉ እንጂ ምድሯ እንኳ ምን ይመስላል ብባል መልስ የለዉም፣ አያዉቃትም ና። ከንቱ ሰው ነዉ ናም።
ሌላኛዋ ኢትዮጵያ ደግሞ ዉብ አገር፣ ማንም በቅጡ ያልተረዳት፣ ጋና ለአለም ብዙ ነገር ማሳወቅ የምገባት፣ ሕዝቦቿ በእኩልነት ነ በጋራ በሰለም ና በስጥቶ መቀበል መርሆ ላይ የተመሰረተ መርህ ላይ የተመሰረተች ና ማንም ሄዶ ልኖርባት የምመኝ አገር፣ ሕዝቦቿ፣ መልካ ምድሯ ማራኪ የሆኑ፣ የዱር እንሥሳዋ፣ እፅዋቷ ገና ተጥንቶ እንኳ ያላለቁ ዉብ ና የተፈጥሮ መስብ የሆነች አገር ናት። ድሞክራሲ ሰፍኖባት፣ ለሁልም እኩል ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የምትለፋ አገር ናት፣ መሪዎቿ ለተቀን ደፋ ቀና እያሉ ነገሮችን ለመቀየር ና ለማስተካከል የለእረፍት ይጥራሉ። ለአለምም ይህችን ዉብ አገር ለማሰዋቅ የለማታከት ይጥራሉ። ለዚህ ጥረታቸዉ በእነሆረስ አይነቶች ያለማታከት ይኮነናሉ፣ ይገሰፃሉ፣ ዉርጅብኝ ይወርድባቸዋል፣ ከሩቅ ቁጭ ብሎ የምሰሩትን ይወንጅላሉ።
ይህች ሁለተኛዋ ኢትዮጵያ እየተነሳች መሆኑዋን ብዙዎች ይመሰክራሉ፣ ያደንቋታል፣ ይገረሙባታል፣ እነ ሆረስ ብቻ ይክዷታል። ለነሱ ይህች ኢትዮጵያ የለችም፣ በእነሱ ጭንቅላት ውስጥ ከተቀረፀችዉ ኢትዮጵያ በስተቀር።
እንደ አገሪቷ ሁሉም ደግሞ ዜጎቿም ከሁለት ምንጭ ነዉ የተቀዱት፣ ከምያወሩት ና ከምሰሩት ልጆቿ ምንጮች። ስለነዚህ ሁለት አይነት ልጆቿ ከዚህ በፊት እዚህ ፎረም ላይ ሀሳቤን ኣካፊዬ ነበር ና አሁን አልደግምም።