ክፍለጦሩ አዳሩን እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሲያደርግ ያደረ ሲሆን በመጨረሻም ሶስት ካምፖችን መደምሰስ መቻሉን የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቃል አቀባይ ገልጿል።
አሶል አካባቢ የሚገኘ የሚሊሻና የፀረ ሽምቅ ካምፕ፣ ሽመልእግር መውጫ የሚገኝ የአድማ ብተና ካመሰፕ እና አለሙ በር አካባቢ የሚገኝ የመከላከያ ኃይል ካምፕ ሙሉ በሙሉ የተመታ ሲሆን አድማ ብተና፣ ፀረሽምቅና ሚሊሻ እጅ የሰጠው እጅ ሰጥቶ የተረፈው ተደምስሷል ያለው ደግሞ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር አዛዥ ፋኖ ሸጋ ጌታቸው ነው። የክፍለጦሩ አዛዥ ጨምሮ እንደገለጸውም ራሱን የመከላከያ ኃይል ብሎ የሚጠራው ገዳይ ቡድን ከተመታው እና ከተማረከው የተረፈው ካምፑን ጥሎ በመፈርጠጥ ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን አቅጣጫ ፈርጥጧል ብሏል።
በአሁኑ ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ አቅጣጫ ያለው መስመሩ የተቋረጠበት ሲሆን አልጣሽ ፓርክ ከመግባትና ወደ ጎረቤት ሱዳን ሀገር ከመሰደድ የዘለለ አማራጭ የለውም ብሏል።
በተልዕኮው በቋራ ኦሜዳድ ክፍለጦር ስር የሚገኙ 100 አለቃ ደጀኔ ብርጌድ፣ ነብሮ ብርጌድ እና ዳግማዊ ቴውድሮስ ብርጌድ እየተሳተፋ ይጋኛል ሲል ሻለቃው ተናግሯል።
@የኢትዮ 251