የአቶ ታየ ደንዳአ ባለቤት፣ ላለፉት አራት ዓመታት ከኖሩበት የመንግሥት ኪራይ ቤት፣ ዛሬ በጸጥታ ኃይሎች ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸውን፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።
ከመንግሥት የኪራይ ቤቶች አስተዳደር እንደመጡ የገለጿቸው ሰዎች፣ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ጠዋት፣ ቤቱን ለቀው እንዲወጡ የሦስት ቀናት ገደብ እንደሰጧቸው የተናገሩት ወይዘሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ፣ ዛሬ ቤቱን እንዳሸጉባቸው አስታውቀዋል።
የመንግሥት የኪራይ ቤቶች አስተዳዳር፣ በጉዳዩ ላይ ምላሽ ባይሰጥም፣ የሕግ ባለሞያ ግን፣ የመንግሥት ክራይ ቤት ውል እና ሕጎች እንዳሉት ገልጸዋል።
ባለፈው ሰኞ፣ በጸጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኀይል በቁጥጥር ሥር የዋሉት የቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ደ’አታ አቶ ታየ ደንዳአ ባለቤት፣ እየኖሩበት ካሉት የመንግሥት ኪራይ ቤት፣ ዛሬ በጸጥታ ኃይሎች ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸውን፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።
በመኖሪያ ቤቱ፣ ላለፉት አራት ዓመታት፣ ከሁለት ልጆቻቸው እና በግጭት ምክንያት ከትውልድ ቀዬአቸው እንደተፈናቀሉ ከገለጿቸው ሌሎች የቤተሰብ አባላት ጋራ ሲኖሩበት እንደቆዩ የተናገሩት የአቶ ታየ ደንዳአ ባለቤት ወይዘሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ፣ “ኹሉንም ዕቃችንን ሳናወጣ በጸጥታ ኀይሎች ታሽልጓል፤” ብለዋል።
ከኪራይ ቤቱ እንዲወጡ የሚያዘው የድርጅቱ ደብዳቤ፣ ትላንት ረቡዕ 10፡00 ላይ እንደደረሳቸው የገለጹት ወይዘሮ ስንታየሁ፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ረፋድ 4፡00 ገደማ፣ የድርጅቱ ሓላፊዎች ከፖሊሶች ጋራ ወደ መኖሪያ ቤቱ በመምጣት አስገድደው እንዳስወጧቸው ተናግረዋል።
እርሳቸው የልጆች እናት እንደኾኑና ባለቤታቸው አቶ ታየም የምክር ቤት አባል እና ገና ተጠርጣሪ እንደኾኑ ገልጸው ሓላፊዎቹን ቢማፀኗቸውም፣ “ሊሰሙን አልቻሉም” ብለዋል ወይዘሮ ስንታየሁ። ለኪራይ ቤቶች አስተዳደር አቤቱታ ለማቅረብ ወደ መሥሪያ ቤቱ ቢሔዱም፣ የተከራይ አቤቱታ ረቡዕ ቀን ብቻ እንደሚያስተናግዱ እንደተገለጸላቸው ተናግረዋል።
https://amharic.voanews.com/a/7398384.html
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4487
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40