Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
TGAA
Member+
Posts: 5747
Joined: 07 Apr 2019, 20:34

የፖለቲካ ፊዝ ( Political satire)

Post by TGAA » 18 Nov 2023, 02:09

የፖለቲካ ፊዝ ( Political satire) እንደ ፖለቲካ የሰነበተና ያረጀ ነው ፡፡ ነገር ግን የፖለቲካ ፍዝ እንደ አቃቂር ማውጫ ለመጠቀም ነው እንጂ የፖለቲካ ቦታን አይዝም ፤ ፖለቲካ ሳይንስም ነው ደግሞም ቁም ነገር ነው ፤ አሁን እየገዘፈና እየተቀጣጠለ ያለው ያማራ ትግል የብዙ ዘመናት ግፍ ህልውና ላይ የተጋረጠን አደጋ ለማሰወገድ አስፈላጊውን መስዋትነትን ከፍሎ የኢትዮጵያንም የስርአት ሰብአዊና ፍትሀዊ ወደ ሆነ ማማ ላይ ለማውጣት የሚደረግ ትልቅ ትግል ነው፡ በአብይ የሚመራው በአጠቃላይ የጸረ ሰሜን በተለይ ደግሞ ጸረ አማራ ፖለቲካን አቃሎ ማየት ትልቅ ስህተት ነው ፤ አብይ ለአምስት አመት ሲያራምድ የነበረው ፖለቲካ ኢትዮጵያ እየዘፈነ በአንደኛ ደረጃ የወያኔን ጉልበት ማምከን ነበር ፤ ይህንን ለማድረግ አማራንና ኢርትራን ተጠቅሞ አሳክቷል ፤ አሁን ደግሞ ወያኔዎችን ከጎኑ አድርጎ አምራን ከዚያ ደግሞ ኢርትራን አመክናለሁ ብሎ እየተፍጨረጨረ ነው፤ ይህ አይሳካለትም ነገር ግን የኢትዮጵያ አንጡራ ተጠቅሞ ህዝብ ለመጨፍጨፍ ወደኋላ እንደማይል በቅርቡ በፓርላም ዲስኩሩ በግልጽ ተናግሯል ፡ ስለዚህ ትግሉን ማቅለል አያስፈልግም ፤ ፖለቲካዊ ፌዝ ቦታ ቢኖረውም ፖለቲካ ግን አይደለም ፡ ይህ ነው 360ና ወደ አበበ በላይ ጋር የሚወስደኝ ፡፡ 360ዎች ገና ህዝቡ የአብይን አታላይ ፖለቲካ ሳይገባው እራሳቸውን ነጥለው በመሄድ ብቸኛ የኢትዮጵያ ህዝብ ልሳን ከሆኑ ቆይተዋል ፤ በአሁኑም ሰአት ትልቅ የኢንፎርሜሽን መስመር በመሆን የአማራ ህዝብ ትግል ድምጽ ሆነዋል ፤ በዚህም ሊመስገኑ ይገባል ፤ ነገር ግን 360 ሀብታሙም ሆነ አበበ በለው ማወቅ ያለባቸው የሚከሄደውን የህዝብ ትግል ለመርዳት በጠላት ላይ ድራማ በመስራትና በማጣጣልና ፤ የአማራ ድልን በአግባቡ እንደመግለጽ የብርሀኑ ጅላን ፤ የአብይን ስም እያነሱ የሰፈር መበሻሽቅ አይነት ፖለቲካ ውስጥ መግባት የለባቸውም ፤ ትግሉን የሚረዳውም አይደለም ፤ ዜናዎች እና ትንተናዎች ትክክለኛና የሚከፈለውን መስዋእትነት ትክክለኛ ግንዛቤ በሚሰጥ መልኩ መሆን አለበት ፤ ኮመዲውን ለኮሜድያን መስጠት ያስፈልጋል ፤ የፖለቲካ ፊዝ መድረክ ስጥቶ ማስተናገድ ይቻላል ፤ ነገር ግን ዩቲዩቡን ከዳር እሰክዳር በሳቅ ሞሙላት ( ሀሳቡ የጠላትን ሞራል ለመጉዳት ቢሆንም ) ሲበዛ ግን ትግሉ እየከፈለ ያለውን ወደፊት የሚከፍለውንም ሚዛንና ግንዛቤ ያሳጠዋል ፤ መሳይ መኮንን በዚህ በኩል የዜና አቀራረቡ ፤ የሚያቀርባቸው ትንተናዎች ፤ የሚጋብዛቸው ፖለቲከኝች እንዲሁን የሚያደርገው አግባብ ያለው አእምሮን በሚፈትን መልኩ የሚቀርቡ ትያቄዎች ሞያዊ ተክህኖ ያላቸው ናቸው ፤ በዚህ ላይ በአማራ የሚገኝ ድሎችን በአግባቡ የሚዘግብበት መንገድ ጋዜጠኝነት በምን አይነት እውቀት መያዝ እንዳለበት የሚያሳዩ ናቸው ፤ አሁንም ሀብታሙና አበበ ለትግሉ እያደረጉትን አስተዋጾ አሁንም የሚያደርጉትን በማደነቅ ነው፡ ወደፊትም ትልቅ አስተዋጾ ያደርጋለው ዋናው ቁም ነገር የፖለቲካ ሳታየርና ፓለቲክ የተለያዩ ስለሆነ ሁለቱን ደባልቀን አሳሳች ግንዛቤ እንዳይኖረን እንጣር ነው ፡፡

Right
Member
Posts: 4785
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: የፖለቲካ ፊዝ ( Political satire)

Post by Right » 18 Nov 2023, 08:39

Excellent observation. Except Minalachew. Please send them your views like I did so that they can correct it. Unbearable and boring. It looks like they missed Ermias Legesse. Biruk Yibas’s popular reading is also gone.
In my view, Messay Mekonen and Ethio Forum have a better presentation.
Habtamu Ayalew is a gifted orator and a very knowledgeable presenter. He better articulate like he used to do before than cheap shots and comedy like presentation which he constantly adopts for some times now. They have to understand that they are the only outlet millions are watching and closely follow.
They may consider: News, political analysis, distinguished guests, allowing viewers to make a phone calls once a week, field presenters etc. Making fun of Birhanu Jula, Abiye Ahmed, Adanech Abebe etc should be left for comedians. Abebe B is Abebe, he tried his best but he doesn’t have it. But I commend him for his efforts.

Post Reply