ከኮሎኔል መንግሥቱ እስከ ኮሎኔል ዐብይ አህመድ---> ብቸኛ ታሪክ የሰራው ኃ/ማርያም ደሳለኝ ብቻ።
ከኮሎኔል መንግሥቱ እስከ ኮሎኔል ዐብይ አህመድ---> ብቸኛ ታሪክ የሰራው ኃ/ማርያም ደሳለኝ ብቻ። እንድሁ የደርግን ስርዐተ መንግስት እንደማስታወሻ በመያዝ በኮ/ል መንግስቱን ጀመርኩት እንጅ ከመንግስቱ በፊት በደርግ የነበሩት እና የአገሪቱ የሆኑት እንደ ጨረቃ ብቅ ብለው ወዲያውኑ የተቀጠፉት ( ተፈሪ ባናቲ፡ አጥናፉ፥ አማን አንዶም) በሁከት የተቀሰፉ ናቸው፤ መንግስቱ ሃይለማርያም እንድሁ ማቄን ጨርቄን ሳይል ተሰደተ እንጅ በክብር ተሰናብቶ የግል ህይወት ሊመራ አልታደለም፤ የጎሳ እና የዘር ደዌ ፈረስ የነበረው መለስ ዜናዊ እንድሁ በአፍላ ዘመነ ሁከተ መንግስቱ ነው የተጠራው። በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህን ያህል መሪዎች በአስከፊ ሁኔታ ሲጠፉ እንደ መዥገር በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ተለጥፈው ደም ሲመጡ የነበሩ ናቸው፤ ታዲያ ሃይለማርያም ደሳለኝ እኔ ሁከት ሰለቸኝ እንካችሁ ብሎ መልቀቁ ( ወዶም ይሁን ተገዶ) በዘመናዊነት ፈርቀዳጅ ፓለቲከኛ ነው። ይግረማችሁ ብሎ አብይ አህመድ የሚባል 7ኛ ገዥ ነኝ አገር ይጨፈጨፋል እንጅ ጭራሽ ይላል። የእርሱ መጨረሻ ምን ይሆን? እየሰራ ያለውን ግፍ መዘርዘር አይቻልም - ከህሌና በላይ ነው።
Re: ከኮሎኔል መንግሥቱ እስከ ኮሎኔል ዐብይ አህመድ---> ብቸኛ ታሪክ የሰራው ኃ/ማርያም ደሳለኝ ብቻ።
ጠብቅ፥አብይም፥ስልጣኑን፥ ለክልል፥ ፫ ይሰጣል፥ ብቻ፥ እናንተ፥እኡታውን፥ ቀጥሉበት፥ ኢያሪኮም፥ በጭሆት፥ ነው፥ የፈረሰው።