Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4487
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Who is to lead the inevitable change & replace Abiy? The true identity of the OPDO leadership and its destructive path

Post by Za-Ilmaknun » 06 Mar 2023, 11:27

Here come Lidetu once again with a good insight in to what is brewing in the current Ethiopia and the way forward. OPDO/OLF is desperately trying to outmaneuver TPLF and ADP and stay the course. The internal contradictions in the current governing leadership are visibly eating the system from within. Abiy is trying to rifle through the cracks to materialize his momentous project of greater Oromia. :mrgreen: Who is to replace the phony man?

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4487
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: Who is to lead the inevitable change & replace Abiy? The true identity of the OPDO leadership and its destructive pa

Post by Za-Ilmaknun » 06 Mar 2023, 14:50

በታሪክ አጋጣሚ የሺሕ ዓመታት አገረ መንግሥት ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያን የመምራት ኃላፊነት በእጁ ላይ የወደቀው ብልፅግና ፓርቲ፣ ይህን ኃላፊነት በአግባቡ የመወጣቱ ጉዳይ ጥያቄ እያስነሳ ነው፡፡ በተለይ በፓርቲው ውስጥ በየጊዜው የሚያገረሸው ተቃርኖና ቁርቁዝ ከራሱ አልፎ ለአገር የሚተርፍ ቀውስ እንዳይፈጥር የብዙዎች ሥጋት ነው፡፡

‹‹የማይተማመን ባልንጀራ በየወንዙ ይማማላል›› እንደሚባለው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፓርቲው ውስጣዊ ችግሮቹን ለመፍታትና ለማጥራት ተወያየ እየተባለ፣ መልሶ በሚታይ ደረጃ በውስጡ ሽኩቻ መስተዋሉ የተለመደ እየሆነ መጥቷል ተብሎ እየተተቸ ነው፡፡

ብልፅግና ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ለሦስት ጊዜ ያህል የውስጥ ችግሮችን ለማጥራት ስብሰባ ተቀመጠ መባሉ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ፓርቲው የፓርቲነት ተክለ ቁመና አለው ወይ? የሚል ጥያቄ ሁሉ እያስነሳ ነው፡፡ በተለይ ዛሬ ታረቁ ተብሎ በማግሥቱ የሚቆራቆዙት የአማራና ኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲዎች ሁኔታ አሥጊነት በሰፊው መነጋገሪያ እየሆነ ነው፡፡ የአማራና የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲዎች ታርቀው የማይቆዩትና በተቃርኖ በተሞላ ግንኙነት ውስጥ የወደቁት ለምንድነው የሚለው የወቅቱ ትልቅ የፖለቲካ ጥያቄ ሆኗል፡፡

https://www.ethiopianreporter.com/116523/

Post Reply