***********************
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት መሠረት በኢፌዲሪ መንግሥት የሚተዳደሩ ተቋማትን ለመጠበቅ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በዛሬው ዕለት ትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ገብቶ ሥራ መጀመሩን ገለጸ።
መንግሥትና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የደረሱባቸውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በትግራይ ክልል የሚገኙ በኢፌዲሪ መንግሥት የሚተዳደሩ አየር ማረፊያዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የቴሌኮም አገልግሎት፣ የባንክ እና ሌሎች ለኅብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጡ የፌዴራል ተቋማት አስተማማኝ ጥበቃ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ቀደም ብሎም በትግራይ ክልል አካባቢዎች በመግባት ኅብረተሰቡን በማረጋጋት ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማድረግ የፀጥታ እና ደህንነት የማስከበር ሥራዎችን እየሠራ መቆየቱ ይታወቃል።
Please wait, video is loading...