አየር መንገዱ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን ወደ ሁለት ከፍ አደረገ
*****************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአርብ ታህሳስ 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን ወደ ሁለት ከፍ ማድረጉን አስታወቀ።
በቀጣይም የመንገደኛ ፍላጎት ቁጥርን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን የሚያደርገውን የበረራ ምልልስ እንደሚጨምር አየር መንገዱ ገልጿል።
ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የአየር መንገዱን ድረ ገፅ እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ ተጠቅመው መመዝገብና ትኬት መቁረጥ የሚችሉ መሆኑንም አስታውቋል።
Please wait, video is loading...