TGAA wrote: ↑10 Oct 2022, 22:49
The leap from ethnocracy to meritocracy has begun unceremoniously. Kudos Berhanu Nega for taking on this herculean task. Those who blamed him last time for the corrupt, ethnically slanted exam result should congratulate Berhanu for taking a major reform to correct the system to provide an equal opportunity for everybody.
TGAA,
ስርዓተ ብቃት (ሜሪቶክራሲ) ያለ ብዙ ሆያ ሆዬ ሰተት ብሎ መጀመሩ ትልቁ ክስተት ቢሆንም ብዙ ተጓዳኝ ውጤቶን ያዘለ ይመስለኛል፣ ይህ በኢትዮጵያ ስርዓተ ትምህርት ዙሪያ የሚሰራው ነገር።
አንድ፣ አቢይን በተመለከተ
አቢይ አህመድ በትምህርት ሚኒስቴር እያገኘ ካለው ድንቅ ውጤት ትልቅ ትምሀር መውሰድ አለበት ። የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ከበርቴ ብቃት አልባዎችን በዙሪያው መሰብሰብ አቁሞ ከማንም ፓርቲና ጎሳ በሜሪቶክራሲ ሚዛን የላቁ መሪና ማኔጀሮችን ወደ ስልጣን ማምጣት ይኖርበታል። ከዚህ ትልቅ ትምህርት የሚወስድ ይመስለኛል!
ሁለት፣ ኢዜማ
ኢዜማ ፓርቲ በመንግስት ውስጥ ተካፍሎ በጭብጥና ፋክት ምን አይነት መሪዎችና ማኔጀሮች ላገር ማቅረብ እንደ ሚችል ማሳያ ሞዴል ሆኖዋል ። በኔ ግምት የብርሃኑ ስኬት አቢይን ብቻ ሳይሆን ኢዜማንም እግጅ የሚጠቅመው ክስተት ነው ።
ሶስት፣ ተማሪዎች
በዚህ ቅጽበት 1 ሚሊዮን የሁለተኛ ደራጃ ተማሪዎች ምናልባትም አንድም ቀን በዪኒቨርሲቲ ዴስክ ላይ፣ በኮሌጅ ክፍል ወስጥ ተቅምጠው የማያውቁ ፣ኮሌጅ ግቢ ገብተው የማያውቁ፣ የኮሌጅ ዶርም ተኝተው ሜስ ሆል ምግብ በልተው የማውቁ ይህ ነው የማይባል የውጣትነት ልምድና ት ዝ ታ እያገኙ ነው ። ከፈተናው ባሻገር ማለት ነው ።
የእኔ ግምትና ፕሪዲክሽን ብዙ ተማሪዎች ከጠበቁት በላይ እስኮር ያደርጋሉ፣ ሚቲቬተድ ይሆናሉ ፣ ፈተናውን ከሚወድቁት መሃልም ብዙዎቹ እንደ ተፈትነው ኮሌጅ የመግባ ምኞታቸው ያድጋል ። ለምን ቢባል የዚያችን ኮሌጅ ግቢና ክፍል ስለረገጡት ። I am sure this was not one of Berhanu's calculation in deciding to give test inside colleges but this will certainly be one of the unintended consequences of the event! ሌላው ቀርቶ ተማሪዎቹ የሁሉንም ኮሌጅ ምግብ ስለ ቀመሱ ኮሌጅ ምርጫቸውን ሁሉ አቅልሎላቸዋል!
አራት፣ ወላጅና ማህበረሰቡ
ይህ አንድ ሚሊዮን ተማሪ ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ እና ማኔጅ የማደግ የሎጂስቲክስ ችሎታና የስንት ሚሊዮን ወላጆች ትኩረት፣ የሚዲያ ትኩረት ሲደመር በጦርነት ወሬ ቋቅ ያለው ህዝባችን ግሩምና አዲስ አላማ ላይ መሰንበቱ እራሱ ለማህበረሰቡ ትልቅ ቴራፒ ነው ።
ብራቮ ውድ የኢትዮጵያ ልጅ ብርሃኑ ነጋ!