Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Thomas H
Senior Member
Posts: 13070
Joined: 27 Jan 2007, 16:30
Location: Kaliti
Contact:

ያልተሳካው የአውሮፕላን ጠለፋ

Post by Thomas H » 11 Dec 2022, 10:59

ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ መስመር ቁጥር 730 ቦይንግ አውሮፕላን 94 መንገደኞችንና 9 የበረራ ሰራተኞችን አሳፍሮ ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል በአስመራ በኩል ወደ አቴንስ፣ ሮም ከዛም ወደ ፓሪስ ለመብረር ዝግጅቱን አጠናቆ በካፒቴን ቀጸላ አማካኝነት ምድርን ለቀቀ። ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሰባቱ እቅዳቸው አውሮፕላኑ ወደሚበርበት አቴንስ ፣ሮም፣ወይም ፓሪስ መጓዝ አልነበረም። ሰባቱ፦
1.ዋለልኝ መኮንን
2.ማርታ መብራቱ
3.አማኑኤል ዮሐንስ
4.ጌታቸው ሀብቴ
5.ታደለች ኪዳነማሪያም
6.ዮሐንስ ፍቃዱ
7.ተስፋዬ ቢረጋ
የሰባቱ ዓላማ አውሮፕላኑን ጠልፈው ወደ አልጄሪያ በማቅናት ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ መንገድ አውሮፕላን ጠልፈው ከወጡት እነ ብረሀነመስቀል ረዳን ከመሳሰሉ ጓዶቻቸው ጋር በኢህአፓ መስራች ጉባኤ ላይ መገኘት ነበር።
መልከ-መልካሟ ማርታ መብራቱ ኮልት 38 ካሊበር ሽጉጥ በላስቲክ ጠቅልላ በጭኗ መካከል በገመድ አስራ ይዛ ገብታለች። አማኑኤል ዮሐንስ ቦምብ ይዟል። የተቀሩትም እንዲሁ በተለያየ መንገድ ሽጉጥ ታጥቀው ነበር አውሮፕላን ውስጥ የገቡት። አውሮፕላኑ ለ13 ደቂቃ ያክል ከበረረ በኋላ…
የሚቀጥለው ጽሁፍ በወቅቱ በአውሮፕላን ውስጥ ተሳፍረው ከነበሩት የአይን እማኝ አቶ አሰፋ አደፍርስ ለጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ ከሰጡት ቃለ-ምልልስ የተወሰደ ነው።
አውሮፕላኑ ለ 13 ደቂቃ ያክል ከበረረ በኋላ ዋለልኝ ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደፊት መጓዝ ጀመረ፣ በእጁ 38 ስፔሻል ሽጉጥ ይዟል። ከተሳፋሪዎቹ አንዱ የነበሩት አቶ አሰፋ አደፍርስ ላይ ዋለልኝ ሽጉጡን በመደቀን the aircraft is hijacked handsup! አላቸው። በወቅቱ ዋለልኝ አቶ አሰፋ anti-hijacker ነበር የመሰሉት። በሁለቱ መካከል በተፈጠረው ግብግብ የመጀመሪያዋ ጥይት ጮኸች። ግብግቡ ተጀመረ….ዋለልኝ በአንቲ-ሃይጃከር በካራቴ ተመቶ ወደቀ፣ ታደለችም ዋለልኝን ለማገዝ ስትሞክር ኃይሉ (anti-hijacker?) በቃሪያ ጥፊ መቶ ጣላት። በዚህ ጊዜ ነበር ማርታ መብራቱ ኮልት ሽጉጧን ይዛ ከኋላ ወንበር የተንቀሳቀሰችው፣ ዒላማዋ ደግሞ ከanti-hijacker አንዱ መቶ አለቃ ተስፋዬ አረሩ ነበር። ይህን የተመለከተው ኃይሉ ማርታን በመሳሪያ መቶ ጣላት፣ ማርታ ላትመለስ ለዘላለሙ አሸለበች። ትንቅንቁ ቀጥሏል……ዮሐንስ የቦንቡን ፒን ስቦታል፣ እጁ ግን ይንቀጠቀጥ ስለነበር የያዘው ቦንብ ከእጁ አመለጠውና ፈነዳ። በፍንዳታው ሰዎች ቆሰሉ። አሁን ከሰባቱ አውሮፕላን ጠላፊዎች ስድስቱ ሞተዋል፣ ታደለች ኪዳነማሪያም ብቻ ቆስላ ተርፋለች። ይህ ሁሉ በሁለትና ሶስት ደቂቃ እድሜ ውስጥ የተፈጸመ ነው። ይህን ሁሉ ያስተናገደው አውሮፕላን ተመልሶ 2:55 ሰዓት ላይ ተመልሶ አዲስ አበባ አረፏል።
➠ ከታች ምስሉ ላይ ያሉት ዋለልኝ መኮንን እና ማርታ መብርሃቱ ናቸው።
#ታሪክን_ወደኋላ