Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

መገፋፋት ይሻለናል ከተባለ ግን ከሁሉም በላይ ሀገር አልባ የሚሆነው ምርጥ ኢትዮጲያዊው ነው። ሀገርህ የት ነው ሲባል ኢትዮጲያ እንዳይል መከባበር አቅቶት አፍርሷታል

Post by sarcasm » 04 Aug 2022, 20:33

ምርጥ ኢትዮጲያውያን ቀንደኛ የኢትዮጲያ ጠላት ናቸው። በርግጥ ጠላትነታቸው ባለማወቅ ወይ በስሜታዊነት የመጣ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ ድንቁርናም አለ።

ኢማጂን እንግዲህ በዚህ ዘመን እራሳቸውን የኢትዮጲያ ጠባቂ ሌላውን ደግሞ ከአፍራሽነት ተጠባቂ አድርገው ይገልፃሉ።
ያልገባችው ግን ዘመኑ መቀየሩ ነው። እነሱ የሀገር ጠባቂ ሌላው ደግሞ የሀገር ስጋት ሆኖ በመሳቀቅ እና በማሳቀቅ የሚኖርበት ዘመን አክትሟል። በጋራ ተከባብረህ በእኩልነት ትኖራለህ ካልሆነ ደግሞ "አብሮ መኖሩ ካላለልን እስኪ እንሞክረው ተለያይተን" ተባብለህ ሀገር ትመሰርታለህ።
እራሳቸው የሀገር አፍራሽ ብለው ይገፉሃል፣ ገፍተውህ ሀገር ለመሆን ስታስብ ደግሞ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላሉ። መገፋፋት ይቅር ሀገር እንታደግ የሚለው ቢቀድም ለኢትዮጲያ ያዋጣታል።

የለም መገፋፋት ይሻለናል ከተባለ ግን ከሁሉም በላይ ሀገር አልባ የሚሆነው ምርጥ ኢትዮጲያዊው ነው። ሌላው ቢቀር አዲስ አበባ ጠቅልላ ፊንፊኔ ስትሆን ፓስፖርት አልባ ዜጎች ሚልዮኖች ይሆናሉ። ሀገርህ የት ነው ሲባል ኢትዮጲያ እንዳይል መከባበር አቅቶት አፍርሷታል። አዲስ አበባ እንዳይል ባለቤት አላት። ይህ ከሚሆን እንደ ህዝብ እንከባበር!!

Please wait, video is loading...