ሰንዳ ለማንም አያዳላም ። ሰንዳ ሌላውን ቆርጦ ሲመለስ ባለቤቱን ይቆርጣል! ሰንዳ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ አይልም። በጎሳ ሰርዓት ውስጥ ሰዎች በሃይማኖት ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በብሄር ተከፋፍለው ይዋጋሉ ። በዘውግ ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በክላን፣ በዞን፣ በወረዳ፣ ባውራጃ ተከፋፍለው ይዋጋሉ ።
የኦሮሞች የባንዲራ ንትርክ ሌላ ጥልቅ የሆነ የክርስቲያንና እስላም ኦሮሞ፣ ያሩሲና ወለጋ ኦሮሞ፣ የሸዋና የእንትን ኦሮሞ ማንነት ልዩነት ውጤት ነው ። ኦሮሞ ወደ ስልጣን በወጣና ትግሉ ሁሉ ስለ ሃብትና ሃይል እየሆነ ሲሄድ ክፍፍሉ እየከረረ መሄዱ ሳይንስ ነው ። ይህ ገና መጀመሪያው ነው ።
በነገራችን ላይ አቢይ አህመድም ከዚህ የባንዲራ ትግል ትምህር መውሰድ አለበት ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔን ያስወገደው በኢትዮጵያ ታሪካዊ ሰንደቅ ስር ተሰልፎ ነው! ከዚህ የሕዝብ ሰንደቅ አላማና ማንነታችን ምልክት እጅህን አንሳ እንለዋለን። ለሱ ለራሱ ጥቅም ስንል! የባንዲራው መዘዝ ብዙ ነው! አይሞትም! አይረሳም!