ሩስያ የዩክሬይንን ዋና ከተማ ኪቭ ዙርያ ጫፍ ላይ ነች - አውሮፓ ግን ዩክሬን ወጥራለች ያላል። ግን ወያኔ ደብረሲና 250 ኪሜ ርቀት ላይ በፋኖ ታንቃ እያለች አድስ አበባ በወያኔ እጅ ልትወድቅ ነው ይሉ ነበር። የትኛውን ከተማ ለመያዝ ይቀርባል? አጃ ኢብ ነው።
ለማንኛውም ጦርነት አስከፊ ነው፤ ምንም በማያውቁ ንጹሃን ሰዎች ህይወት ላይ ጥሎት የሚያልፈው ጠባሳ ቀላል አይደለም። እኛ አፍሪካኖች ደግሞ ጦርነት በጦርነት ህግ ሰላማይመራ ሰብዐዊ ቀውሱ እጅግ ዘግናኝ ነው። ለውጭ አገር ጆሮ ሲባልም ጥፋቱ ይብሳል። ብዙ መሰልጠን ይገባናል። በ2 ቀን የሩስያ ጦርነት ያለቀውን እና በግማሽ ቀን አሳጊታ ወይም ቦሩ ሚዳ የተጨፈጨፈውን ማመዛዘን ይገባል። የጦረኞችን እጅ ይዞ ለፍርድ በማቅረብ ዕልቂት ማቆም ብልህነት ነው።