5፤ በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን የሚገኘው ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ የኦሮሞ ነጻነት ታጣቂዎች በፈጸሙበት ጥቃት ሳቢያ ከየካቲት 2 ጀምሮ ምርት ማቆሙን ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ሰምቻለሁ ሲል ብሉምበርግ ዘግቧል። የቡድኑ ታጣቂዎች በፋብሪካው ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ እንደቆዩ የገለጸው ኮርፖሬሽኑ፣ በቅርቡ የፋብሪካውን የሸንኮራ አገዳ እርሻ እና ትራክተሮችን በእሳት ማጋየታቸው ለምርቱ መቆም ምክንያት መሆኑን ገልጧል። ባካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ሳቢያ ፋብሪካው ለረጅም ጊዜ ነዳጅ ማስገባት እንዳልቻለ የገለጸው ኮርፖሬሽኑ፣ ፋብሪካው ምርት ማቆሙን ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት በማሳወቅ ምላሽ እየተጠባበቀ መሆኑን ተናግሯል። የአንጋፋው ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ አማካይ ዓመታዊ የስኳር ምርት 270 ሺህ ቶን ይደርሳል።
6፤ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን የሚገኘው ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ንብረት የሆኑ 2 ሰብዓዊ አገልግሎት ሰጭ አምቡላንሶች ሰሞኑን በኦነግ ታጣቂዎች በኃይል እንደተወሰዱበት ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ለሰብዓዊ አገልግሎት በተሠማሩ የማኅበሩ አምቡላንሶች ላይ የተፈጸመው ድርጊት ኢትዮጵያ ያጸደቀችውን ዓለማቀፉን የጄኔቫ ኮንቬንሽን የሚጥስ ነው።
[ዋዜማ ራዲዮ]