Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Noble Amhara
Senior Member
Posts: 13728
Joined: 02 Feb 2020, 13:00
Location: Abysinnia

The Lords Prayer in Geez, Tigrinya, Amharic, Sodo Guragegna

Post by Noble Amhara » 29 Jan 2022, 20:21


Horus
Senior Member+
Posts: 42893
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: The Lords Prayer in Geez, Tigrinya, Amharic, Sodo Guragegna

Post by Horus » 30 Jan 2022, 00:21

Noble Amara,
ጥቂት እርማቶች (ኮምፒዩተሩ የጉራጌኛ ፊደል ገበታ ፕሮግራምድ ስላልሆነ) ያሳሳተውን ላሳይህ
መጀመሪያ የቋንቋው ስም ክስታኔኛ ነው ። ሶዶ የቦታ ስም ነው እንጂ የህዝቡም የቋንቋውም ስም አይደለም፣ ሕዝብ በቦታ ሊጠሩ ይቻላል ፣ በዚያ መሰረት ሶዶ ጉራጌ ከተባለ ትክክል ነው ። ሶዶ ክስታኔ ማለት ስህተት ነው ። ሶዶ ጉራጌ ወይም ክስታኔ ጉራጌ ማለት ትክክል ነው ። ቋንቋው ግ ን ሁልግዜ ክስታኔኛ መባል አለበት ። ሶዶኛ የሚባል ቋንቋ የለም ።
የአማርኛው 'እ' በክስታኔኛ 'ኧ' ነው ፤ ምሳሌ 'እኔ' = 'ኧዲ' ፤ 'እመጣለሁ' = 'ኧመጣው' ' እቀመጣለሁ' = 'ኧቶናው'
የአማርኛው 'ይ' በክስታኔኛ 'ዬ' ነው፤ ምሳሌ 'ይሁን' = 'ዬሁን' ኬር ዬሁን። 'ስምህ ይቀደስ' = 'ስምደ ዬትቀደስ'
'አሜን = 'አሚን' ምሳሌ 'ኬር ዬሁን አሚን'

እግዚአብሄር ይስጥልኝ ! እዝጌር ያብሊ !

Post Reply