ብአዴኖች በማያዝዙበት ጦርነት ለምን መግለጫና ማብራሪያ ለመስጠት እንደሚሽቀዳደሙ ነው የሚገርመው። ኦህዴድ ደግሞ ሁሌም እነሱን ካስዋሸ በኋላ ተቃራኒውን በተግባር ሲፈፅም ይታያል።
በነገራችን ላይ አንድን የፖለቲካ ቡድን ታማኝ ባሪያ ለማድረግ ስትፈልግ፥ በመጀመሪያ ወጣሁበት ወይም እወክለዋለሁ ከሚለው ማህበራዊ መሠረቱ ትነጥለዋለህ። ይህንን ከማሳኪያ መንገዶች አንዱ ደግሞ ተአማኒነቱን በመሸርሸር ለምንም ነገር የማይታመን ማድረግ ነው። ኦህዴድም ብአዴንን ለዚህ ነው በየመድረኩ ሲያስለፈልፈው ይቆይና፥ በመጨረሻም እሱ በተግባር ተቃራኒውን ይዞ ብቅ ይላል።
ቢያንስ ወያኔ ከወረረው የአማራ ግዛት ሙሉ በሙሉ ባልወጣበት ሁኔታ "ባለህበት እርጋ" የሚል ትዕዛዝ ሲፈፀም፥ "ለምን⁉" የማለት አቅም እንኳ በሌላቸው ነገር ላይ ነው ተንደርድረው መግለጫ ሲሰጡ የሰነበቱት።
የአማራ ህዝብ ሆይ‼ ከሰኔ እስከ ታህሳስ የሆነልህንና የሆነብህን ኦዲት አድርግና፥ ትርፍና ኪሳራህን አስልተህ ስታበቃ፥ ለዘመናት እንደዕብድ ስንጮህና ስንነግርህ ያለመስማትህን ውጤት ተመልከተው።
ቢያንስ ከሰኔ በፊት ይዘኸው የነበረው ይዞታህ፥ ዛሬ በከፊል የለም። የውድመቱን ነገር እየኖርክበት ስላለ ምኑን እንደአዲስ እነግርሃለሁ⁉
ዴቭ ዳዊት።
Please wait, video is loading...