Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

የአሁን መረጃዎች!

Post by Ejersa » 31 Oct 2021, 10:06


Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

Re: የአሁን መረጃዎች!

Post by Hameddibewoyane » 31 Oct 2021, 10:08

በደሴ ግንባር እና በኮምቦልቻ ከፍተኛ ውግያ እየተደረገ ሲሆን ሰራዊታችን ከአማራ ልዩ ሀይል እና ከአማራ ህዝብ እንዲሁም ፋኖ ጋር በመተባበር ይዞታውን ወደ ጭፍራ ወረባቦ እና በጋሸና በኩል በማስፋፋት ላይ እንደሚገኝ ታውቋል::

Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

Re: የአሁን መረጃዎች!

Post by Ejersa » 31 Oct 2021, 10:19

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሓት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ደሴና አካባቢዋን ለመውረር ከየአቅጣጫው ተሰባስቦ አሰፍስፎ የነበረውን ወራሪ የሽብር ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የደሴን ከተማ በወገን እጅ እንዳለች ማስቀጠል መቻሉን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።

የደሴ ከተማ እና የአካባቢው ነዋሪዎች የሽብር ቡድኑን የፈጠራ ወሬ ባለመስማት አካባቢውን ጸንቶ እንዲጠብቅና ለግንባሩ ሰራዊት ሲያደርጉት የነበረውን ደጀንነት እንዲያስቀጥሉም ተጠይቋል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል፡፡

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም።

በጢጣ በኩል ሰብሮ በመግባት የደሴ ከተማን ለመቆጣጠር የሞከረው አሸባሪው የህወሓት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል።

የመጣውን ኃይልም ደሴ ከተማ ከመግባቱ በፊት ሙሉ በሙሉ ባለበት ማስቀረት መቻሉን በወሎ ግንባር ወራሪውን ኃይል እያጸዱ የሚገኙ የመከላከያና ደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለመ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት ካለመረዳት የመነጨ እንደሆነ አስታውቀዋል።

በግንባሩ የተሰለፉ የሰራዊት አመራርና አባላትም ወራሪውን ኃይል ለአንዴና መጨረሻ ለማጥፋት አኩሪ ተጋድሎ እየፈጸሙ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

በኩታበር በኩል አሰፍስፎ ደሴን ለመውረር የመጣው ወራሪ ኃይልም ምንም ማድረግ እንዳይችል ተደርጎ መደቆሱን ለኢዜአ ገልጸዋል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብተው የነበሩ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂዎችም ባሉበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው መሸኘታቸውን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ደሴና አካባቢዋን ለመውረር ከየአቅጣጫው ተሰባስቦ አሰፍስፎ የነበረውን ኃይልም አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የደሴን ከተማ በወገን እጅ እንዳለች ማስቀጠል መቻሉን ገልጸዋል።

የደሴ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ቡድኑን የአፈሳ ወሬ ባለመስማት አካባቢውን ጸንቶ እንዲጠብቅና ለግንባሩ ሰራዊት ሲያደርጉት የነበረውን ደጀንነት እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።

በግንባሩ ያሉ የሰራዊት አባላት የጥፋት ቡድኑን ማጽዳት ይቀጥላሉ ያሉት ምንጮቻችን በቅርብ ጊዜም ይህኑ የኢትዮጵያ ጠላት የሆነ ወራሪ ኃይልም እስከወዲያኛው የሚሸኙበት ቀን ሩቅ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል።
Ejersa wrote:
31 Oct 2021, 10:06

Abe Abraham
Senior Member
Posts: 14414
Joined: 05 Jun 2013, 13:00

Re: የአሁን መረጃዎች!

Post by Abe Abraham » 31 Oct 2021, 10:41

Every inch is extremely costly for the Tigrés. Thousands of them have died and are dying !

Courtesy of ethioscience





Weyane.is.dead
Member+
Posts: 6796
Joined: 19 Oct 2017, 11:19

Re: የአሁን መረጃዎች!

Post by Weyane.is.dead » 31 Oct 2021, 10:57

That's very gruesome. Please put a warning at least.
Abe Abraham wrote:
31 Oct 2021, 10:41
Every inch is extremely costly for the Tigrés. Thousands of them have died and are dying !

Courtesy of ethioscience





Post Reply