በሌላ በኩል ደግሞ ህወሃትን ሲነኩበትና ጥቅሙ የተነካ ሲመስለው እንደ ቀንድ አውጣ ወደ ሼሉ ይገባና የትግራይ ብሄርተኝነትንና የህወሐት ምልኪን ያነሣል። ሲጠቀም ኢትዮጵያዊ፣ ሲቸገር ትግራዊ ይሆናል። በዚህ ስምንት ወር የታየውም ይሔ ነው። ሕዝቡ ራሱን ወያኔ አደረገ። የኢትዮጵያን መከላከያ እንደ ሌላ ሀገር ወታደር ቆጠረው። ከኢትዮጵያ ጋር ሆኜ ከምኖር ከሕወሃት ጋር ሆኜ ልሙት አለ። እርዳታውን ይፈልገዋል፤ የኢትዮጵያን የቴሌ፣ የመብራት እና የጤና አገልግሎቶችን ይፈልጋል። ራሷን ኢትዮጵያን ግን አይፈልጋትም። ላሚቱን እየደበደበ ወተቷን ማለብ ይፈልጋል። የተጠቀመው ጥቂቱ ትግራዋይ ቢሆንም ብዙሃኑ ግን ስነ ልቦናዊ ጥቅም እንዳገኘ ይሰማዋል።
https://www.goolgule.com/tigray-blessings-and-curse/