**ወንድወሰን ተክሉ** (Wondwossen Teklu Wondelove)
«እኛ መጀመሪያኑ ወደ ትግራይ የገባነው ትግራይን በOccupation ይዞ ለመቆየት ሳይሆን ሰራዊታችንን እና የጦር መሳሪያዎቻችንን ለማውጣት ነው» አቢይ አህመድ ዛሬ ጥያቄ እንዲጠይቁ ሳይሆን የተነገራቸውን አድምጠው በማጨብጨብ እንዲያስተጋቡ ለጠሯቸው በአስሮች ለሚቆጠሩ «ጋዜጠኞች» ከትግራይ የወጡበትን ምክንያትና መንገድ ሲያስረዳ የተናገረው ነው፡፡
እንደ አቢይ መራሹ መንግስት ግልጽ ውሳኔና አቋም መሰረት ባለፈው ኖቬምበር አራት ቀን 2020 ላይ «የህግ የበላይነትን ለማስከበርና የትግራይን ህዝብ ከጁንታው አገዛዝ ነጻ ለማውጣት » ተብሎ ወደ ትግራይ የዘመተው የመከላከያ ሰራዊት ዋና እና ብቸኛ ግብ በትግራይ ያለውን የመከላከያ ሰራዊትና የተለያየ የጦር መሳሪያን ለማውጣት ብቻ እና ብቻ ነው በሚል ከደመደመ በኃላ ዛሬ ያንን ሚሽን በማጠናቀቁ ጦሩ ከትግራይ ሙሉ በሙሉ በመውጣት ክልሉን ለትህነግ አስረክቧል ያለ ሲሆን በዚህም መሰረት «ከዛሬ ጀምሮ በትግራይ ላለው ማንኛውም ጉዳይ የፌዴራሉ መንግስት አያገባውም » በማለት በግልጽ አውጇል፡፡
ይህ አቢይ መራሹ መንግስታዊ እወጃ ዘርዘር ተደርጎ ሲታይና ጠቅለል ተደርጎ ትርጉሜውን ምን ማለት ነው ብሎ ሲጠየቅ የምናገኘው መልስ «መጀመሪያም ትግራይ የገባነው ለህዝቡና ለአጠቃ ኢትዮጲያዊ ሉዓላዊ ግዛት ብለን ሳይሆን በትግራይ ያለውን የመከላከያ ሰራዊታችንን እና በጁንታው እጅ የገባውን የጦር መሳሪያን ብቻ በማውጣት ክልሉን አሸባሪው ጁንታ እንደፈለገ እንዲያደርገው ለቅቀንለት ለመውጣት ነው» የሚል መልስ ይሆንና ይህ መልስ ደግሞ በአጭሩ ሲጠቃለል ትግራይን ዲፋክቶ እስቴት በማድረግ ከኢትዮጲያ መገንጠል ማለት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
የአቢይ መራሹ የኦህዴድ ብልጽግና መንግስት የትግራይን ግዛት ከኢትዮጲያ የመገንጠሉን እርምጃ ዛሬ ያለምንም አንጃ ግራንጃ በግልጽና በአደባባይ ፍርጥ አድርጎ የገለጸ ሲሆን ይህንን አስደንጋጭ እርምጃውን ግን ኢትዮጲያዊያኑ ማወቅ በሚገባቸው መጠን ተረድተው አላወቁትም ወይም ያወቁትም ቢሆኑ በኢትዮጲያ ግዛታዊ ሉዓላዊነት እና በአቢይ ስልጣን መካከል አንዱን መምረጥ ተምታቶባቸው ዝም ብለው እያዩት ያለ .....Read more
Please wait, video is loading...