Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Wedi
Member+
Posts: 8649
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

ከሁመራ እንደወጡ የቀሩት የአባ ሓጎስ ነገር!!!

Post by Wedi » 21 Dec 2020, 07:55

:lol: :lol: :lol:
Asfaw Abreha
·
አባ ሓጎስ ____

"የሰሜን ዕዝ ከወያኔ ጋር ወግኗል" ሲሏቸው አሜን ብለው የተቀበሉ የወያኔ ቀፎዎች በርካታ ነበሩ።

_ ታዲያማ የመከላከያ ሰራዊቱ የወያኔን የኩታራ ጀሌ ደረማምሶ ሁመራ ሲገባ አንዱ የወያኔ ቀፎ ሁነቱን በተቃራኒው ነበር የተቀበለው _ _ ከወያኔ ጋር ወገነ ተብሎ የተነገረው የሰሜን ዕዝ ጦር የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን ድል አድርጎ ሁመራ የገባ መስሎታል ለካ!!

ይህ ሰው( አባ ሓጎስ ) አስፋልት መንገዱ ላይ ጎራዴ ይዞ 'እልል' እያለ ሰራዊቱን ከተቀበለ በኋላ የተወሰኑትን ወታደሮች ወደ ንግድ ቤቱ ( ልኳንዳ ቤት ) ወስዶ ምሳ እየጋበዝ ...

" እና እንዴት ነው ? አሃዳዊያኑን ጨረሳችኋቸው አይደል ? ጦርነቱስ አለቀ ? " እያለ ወታደሮቹን አከታትሎ ይጠይቃቸዋል ።

ወታደሮቹም " ደብረፂዮንን ካልያዝን የሚያልቅ ጦርነት የለም !! " ብለው ሲሉት ..

ሰውየው በድንጋጤ " በስመአብ ወልዴ ! ምን ? .... ነይማ ማነሽ ! ካልጫው፣ ከቀዩ ፣ ከጥብሱ ፣ ከዱለቱ ፣ ከቅልጥሙ ጨመርመር አድርጊላቸው እስኪ .. እኔ የሚጠጣ ነገር ላምጣላቸው " ብሎ እንደወጣ ሳይመለስ ቀረ ።

አሁን ሱዳን _ ሃምዳይት አለ !!

እኔ ሁመራ በነበርኩበት ጊዜ የአባ ሓጎስ ምላስ እና የልኳንዳ ቤታቸው 'ምላስና ሰንበር' እጅግ የተለዩ ነበሩ !!!