Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

ወያኔ ሮኬት ከማስወንጨፍ ወደ ድንጋይ በወንጭፍ ተቀይሯል!

Post by Ejersa » 19 Nov 2020, 14:45

አይ ወያኔ! ሮኬትና ሚሳኤል #አናርከፈክፍባችኋለን እያሉ ሲዝቱና ሲያስፈራሩን የነበሩት ከግብፅ በተበደሯቸው #ተኳሾች ኖሯል ለካ ነገሩ እንደዚህ ነው። ከጫካ ጀምሮ ወያኔዎች ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችን የማንቀሳቀስ ዕውቀት ሆነ ብቃት የላቸውም። ሄሊኮፕተር በድንጋይ ማረክን ሲሉ እንጂ ሄሊኮፕተር አብራሪ ያላቸው አይመስለኝም። አንድ ትግራይ ጀት አብራሪነት ቢያስተምሩት ትምህርቱ ናላውን አዞረው አሉ። እንዳይደርስ የለምና እንደ ምንም ብሎ ለመመረቅ በቃ። በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ የተገኘው ማን ቢሆን ጥሩ ነው? መለስ ዜናዊ! የተመራቂው ውጤት ምን ቢሆን ጥሩ ነው? ከተመራቂዎቹ ሁሉ የመጨረሻ ዝቅተኛ ውጤት። በአጠቃላይ ወያኔዎች ትላልቅ የጦር መሣሪያዎችን መዝረፍ እንጂ መስረቅ አይችሉም። በኢትዮጵያ አሉ የተባሉ ሚሳኤሎችን ዘርፈው ከወሰዱ በኋላ የሚሳኤሉ መቆጣጠሪያ አዲስ አበባ መሆኑ ትዝ ያላቸው ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ነው።

ከሰሜን ዕዝ ላይ ብዛት ያላቸው ሮኬቶች ከመዝረፋቸው በፊት ግን ተኳሾችን ከግብፅ መንግስት ተበድረው ኖሯል። በጥቅምት ወር ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት የግብፅ ወታደሮች መካኸል ዘጠኝ ወታደሮች በቦሌ ይሁን በሁመራ ሾልከው መቀሌ ገብተው ኖሯል። የግብፅ መንግስት ትላንት ዘጠኝ ዜጎቹን ከትግራይ ማስወጣቱን Ahram Online ዘግቧል። አሁን ከውስጥ አዋቂዎች በደረሰኝ መረጃ መሰረት ትላወደ ሀገራቸው ከተሸኙት ግብፃውያን ውስጥ የተወሰኑት የወያኔዎች ብቸኛ ሮኬት ተኳሾች ኖረዋል ለካ። ስለዚህ ወያኔ ሮኬት ከማስወንጨፍ ወደ ድንጋይ በወንጭፍ ተቀይሯል።

Fiyameta
Senior Member+
Posts: 21339
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: ወያኔ ሮኬት ከማስወንጨፍ ወደ ድንጋይ በወንጭፍ ተቀይሯል!

Post by Fiyameta » 19 Nov 2020, 14:56

የዓድዋው ወያኔ ኮሎኔል ሺሻይ አሟሟት





ከወያኔ እብሪትና የአለማወቅ ታሪኮች መካከል የኮሎኔል ሺሻይ አሟሟት ተጠቃሽ ሊሆን የሚችል ነው። ከህወሃት የኣመራር አባላት የአንዱ ወንድም (ቢተው በላይ) የነበረው ኮሎኔል ሺሻይ በትግሉ ወቅት የጉና ክፍለሰራዊት አዛዥ ነበር። ከደርግ ውድቀት በሁዋላ ኮሎኔል ሺሻይ የኢትዮጵያ አየር ሃይል መስርያ ቤት ዉስጥ የሄሊኮፕተር ኦፐሬሽን አዛዥ ሆኖ ተመደበ። ይህ ስልጣን ሲስጠው ግን ኮሎኔል ሺሻይ ሄሊኮፕተር ተሳፍሮ ያውቃል እንጂ ስለ ሄሊኮፕተር አንዳችም እውቀት አልነበረውም። :lol:

ታሪኩ እንዲህ ነበር.......

ኮሎኔል ሺሻይ የዉግያ ሄሊኮፕተር ኣዛዥ መሆኑ ካልቀረ ተብሎ ሄሊኮፕተር የማብረር ትምህርት መከታተል ይጀምራል። አሰልጣኞቹ የደርግ ተሸናፊ መኮንኖች ነበሩ። ሰልጣኞች ደግሞ አሸናፊዎች። መምህራን ከልብ ሊያስተምሩ አልቻሉም። ተማሪዎች ደግሞ በመምህሩ ላይ የበላይነት ካላሳየሁ ይላሉ። አስተማሪ ደፍሮ ተማሪውን አይናገረውም። ከሺሻይ መምህራን አንዱ ሻምበል እሸቱ ገመቹ ይባላል። ሺሻይ የዚህ ሰው አለቃ ሆኖአል። ....... በዚያን ወቅት ግን መምህራን ሺሻይን "አልቻልክም! ወድቀሃል! ቻው!" ሊሉት አይችሉም ነበር። ሻምበል እሸቱ ገመቹኡ ይህን ቢያደርግ "ኦነግ ነህ!" እንዳይባል ይሰጋ ነበር። ስለዚህ መምህራን ሁሉ ሺሻይን እሹሩሩ እያሉ የሄሊኮፕተር ተዋጊ ለማድረግ መከራቸውን እያዩ ነበር።

ይህ በእንዲህ እያለ የኤርትራ ጦርነት ተከሰተ። ከእለታት አንድ ማለዳ ወደ ቡሬ ግምባር ሄሊኮፕተር እንዲላክ ትእዛዝ ይመጣል። ኮሎኔል ሺሻይ ባስቸኳይ ሻምበል እሸቱን ያስጠራል። ሻምበል እሸቱ ገመቹ ግን በአከባቢው ሳይገኝ ቀረ። ምናልባት ሻይ ለመጠጣት ወደ ክበብ ጎራ ብሎ ሊሆን ይችላል። ወዴያ ወዲህ በማለት እሸቱን ማፈላለግ በተቻለ። ሺሻይ ግን ይህን አላደረገም። እራሱ ወደ ሄሊኮፕተሯ ገብቶ ቀሰቀሳት። በህጉ መሰረት ሽሻይ የበረራ ትምህርቱን ያልጨረሰ እንደመሆኑ ሄሊኮፕተር ብቻዉን ይዞ መሄድ የሚፈቀድለት አልነበረም። ልክ እንደ ሚኒ ባስ ሄሊኮፕተሯን አስነስቶ ወደ ቡሬ ጭልጥ አለ። :lol:

ሄሊኮፕተር እየነዱ መሄድና፣ እየነዱ መዋጋት ግን ለየቅል ነበሩ። ገና ቡሬ ከመድረሱ የሻእቢያ ፀረ አይሮፕላን ሚሳይሎች "እንኳን ደህና መጣህ!" ሲሉ የሞቀ አቀባበል አደረጉለት። ሺሻይና ጓደኞቹ ከነሄሊኮፕተራቸው አየር ላይ ጋዩ። ወርደዉም አሰብ ላይ ተከሰከሱ።
:oops: የኤርትራ ወታደሮች ሄሊኮፕተሯን ሲፈትሹ ሰዎቹ በመቃጠላቸው ማንነታቸው ለመለየት የሚቻላቸው አልነበረም። የጦር አይሮፕላን አብራሪዎች ግን ከብረት የተሰራች መታወቅያ አላቸው። ያንን የብረት መታወቅያ ሲፈልጉ "ሻምበል እሸቱ ገመቹ" የሚለው ያገኛሉ። ምክንያቱም እሸቱ ለበረራ ዝግጁ ስለነበር የብረት መታወቅያዉን እዚያው ትቶአት ኖሮአል። በነጋታው የኤርትራ ሬድዮ ሻምበል እሸቱ ገመቹ የተባለ ፓይለት ከነሄሊኮፕተሩ ተመቶ መውደቁን ዜና ሲያውጅ ሻምበል እሸቱ በሞቀ ኣልጋ ዉስጥ ነበር።
:lol: :lol: :lol: :lol:


Post Reply