Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 40355
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 23 Aug 2020, 03:04
ዛሬ ኦርቶዶክስ ፍልሰታ ነው ።
ነሃሴ (ናሴ) 15 በጉራጌ የምጅር (የደመራ) መትከያ ቀን ነው።
አሁን ሰዉ ሁሉ ራስ ወዳድ ሆነ እንጂ እኛ ልጆች ሆነን በምጅር መትከያ ቀን ማንም ሰው ዛፉ ለደመራ (ለምጅር) ቢቆረጥ አይከለክልም። ልጆችም የማንም ዛፍ ለምጅር ቢቆርጡ ፈቃድ አይጠይቁም።
ዛፉን (ቀጥ ያሉ ወጣት ዛፎችን) ቆርጠን ቆዳውን ከላጥን (እንዲደርቅ) በኋላ የደመራው የምጅሩ አጥንት ተሸካሚ የሆኑትን የምጅሩ እስኬሌተን በትልቅ ሆያ ሆዬ ጭፈራ የምንተክለው ዛሬ ነው፣ ናሴ 15!
ከዛሬ እስከ መስቀል 1 ወር አለ ። በመሃሉ ያው የዛሬ 2 ሳምንት 'አክራሚ' እንቁጣጣሽ አለ ። ከዚያም ካክራሚ ማግስት እስከ ደንጌሳት የሴቶች ፤ 'ኢምር ኢምር' የብርሃን ዘፈን በምጅሩ ዙሪያ ማታ ማታ አለ ... እያለ ለሴቶቹ መስቀል፣ ለልጆቹ መስቀል፣ ለታላቁ መስቀል፣ ላዳብና፣ ላዳምና እንደርሳለን።
ማለትም ለቅድመ ኦርቶዶክስ ጉራጌ የዘመን መለወጫው አዲስ አመት በዓል የ15 ቀን ፌስታ ነበር ፤ ከአክራሚ (እንቁጣጣሽ) እስከ መስቀል !!!
በጉራጌ ቋንቋ አክራሚ (ወይም የኬርማይ) ማለት ቅዱስ ቀን ማለት ነው። የቅዱስ ዮሃንስ ወይም የእንቁጣጣሽ እለት ቅዱስ ቀን እንለዋለን ።
Last edited by
Horus on 23 Aug 2020, 04:09, edited 3 times in total.
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 40355
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 23 Aug 2020, 03:25
ሰዎች ልብ የማይሉት ነገር መስቀል ለጉራጌ ሕዝብ የክርስትናም የእስልምናም ሃይምኖታዊ በዓል አይደለም። መስቀል የሁሉም ጉራጌ ኦርቶዶክስ፣ ሙስሊም፣ ኦሪታዊ ሁሉ ያዲስ አመት እጅግ ግዙፍ በዓል፣ ባህል፣ ካልቸርና ሕዝባዊ ማንነት መገለቻ ደስታ ሁሉ ደስታ፣ የበዕላት ሁሉ በዓል ነው !!! ወደ ፊት በመስቀልና በገና መሃል ያለውን የእምነትና ባህላዊ ትስስር የምለውን እላለሁ !!
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 40355
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 23 Aug 2020, 03:55
እዚህ ውስጥ ሴቶች በቡድን የሚሰሩት የሴቶች ዉሳቻ ይባላል፣ የሴቶች ደቦ ማለት ነው። ለምሳሌ የልጆች ከብት ማገድ ደቦ ዎጀ ይባላል። ሌላው ቀርቶ የበዕል እንጨት ፈለጣ ፣ ጌሾ ወቀታ ሁሉ በደቦ ነው የሚሰራው ።
-
Degnet
- Senior Member+
- Posts: 25078
- Joined: 16 Feb 2013, 11:48
Post
by Degnet » 23 Aug 2020, 04:41
Horus wrote: ↑23 Aug 2020, 03:04
ዛሬ ኦርቶዶክስ ፍልሰታ ነው ።
ነሃሴ (ናሴ) 15 በጉራጌ የምጅር (የደመራ) መትከያ ቀን ነው።
አሁን ሰዉ ሁሉ ራስ ወዳድ ሆነ እንጂ እኛ ልጆች ሆነን በምጅር መትከያ ቀን ማንም ሰው ዛፉ ለደመራ (ለምጅር) ቢቆረጥ አይከለክልም። ልጆችም የማንም ዛፍ ለምጅር ቢቆርጡ ፈቃድ አይጠይቁም።
ዛፉን (ቀጥ ያሉ ወጣት ዛፎችን) ቆርጠን ቆዳውን ከላጥን (እንዲደርቅ) በኋላ የደመራው የምጅሩ አጥንት ተሸካሚ የሆኑትን የምጅሩ እስኬሌተን በትልቅ ሆያ ሆዬ ጭፈራ የምንተክለው ዛሬ ነው፣ ናሴ 15!
ከዛሬ እስከ መስቀል 1 ወር አለ ። በመሃሉ ያው የዛሬ 2 ሳምንት 'አክራሚ' እንቁጣጣሽ አለ ። ከዚያም ካክራሚ ማግስት እስከ ደንጌሳት የሴቶች ፤ 'ኢምር ኢምር' የብርሃን ዘፈን በምጅሩ ዙሪያ ማታ ማታ አለ ... እያለ ለሴቶቹ መስቀል፣ ለልጆቹ መስቀል፣ ለታላቁ መስቀል፣ ላዳብና፣ ላዳምና እንደርሳለን።
ማለትም ለቅድመ ኦርቶዶክስ ጉራጌ የዘመን መለወጫው አዲስ አመት በዓል የ15 ቀን ፌስታ ነበር ፤ ከአክራሚ (እንቁጣጣሽ) እስከ መስቀል !!!
በጉራጌ ቋንቋ አክራሚ (ወይም የኬርማይ) ማለት ቅዱስ ቀን ማለት ነው። የቅዱስ ዮሃንስ ወይም የእንቁጣጣሽ እለት ቅዱስ ቀን እንለዋለን ።
Yetem yekebral,Mekelle lemsale gen Merkato slemawkew des yelu neber(ye lijnet gize)
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 40355
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 25 Aug 2020, 01:32
7 ጎጎት ዶቢ እነ መሃል አምባ፣ እነኬላ እነሱተን እነኑረና እነ ኧሽከዲየ
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 40355
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 25 Aug 2020, 04:09
እጅግ ወብ ከሆኑት አዲስ ነጠላዎች አንዱ !!! ጉራጌ የካልቸር ባህር !! የጥበብ ፋፍሪካ !!!