አሁን የሚታየው የፖለቲካ ፉክቻ፣ ሹም ሽር፣ ሹመትና ድራማ ሁሉ ለሚቀጥለው ምርጫ የሚደረግ ዝግጅት ነው።
ተፎካካሪ የሚሆን ሁሉ ወይ ታስሯል፣ ወይ ተዳክሟል፣ ወይ ታፍኖአል።
ታከለ ካዲሳባ የተነሳው በመሬት ሌብነት ሙስና ስለተጨማለቀ እና አዲሳባን ኦሮማይዝ ለማፍረግ በተያዘው ዴሞግራፊ ለውጥ ሳቢያ ፒፒ በፍጹም ያዲሳባን ድምጽ ስለማያገኝ ይህ ሩጫ ሁሉ ያን ለማስተካከል ነው።
አቢይና ፒፒ ሙሉ ትኩረታቸው አዲሳባን እንዴት እንደ ሚያሸንፉ መስራት ላይ ነው ። የፖለቲካ ሎጂክ ማለት እንደ ሚከተለው ነው ።
ያቢይና ፒፒ ፍጹም አላማ የዛሬ አመት በሆነ ምርጫ ስልጣን መያዝ (መቀጠል)፣ ብሎም ለ10 አመት ቢያንስ መግዛት ይህ ነው ። አሁን ያለው ድራማ ሁሉ ያንን እውን ለማድረግ ነው
ይህን ሁሉ ለማድረግ ገንዘብ ያስፈልጋል፣ ለሁለት ነገር ። አንድ ፣ ያዲሳባ ፕሮጀክቶችን ጨርሶ ህዝቡን ለማማለል፤ ሁለት፣ ለምርጫ ማካሄጃ ።
ያቤቤ ሚሽን አዲስ አበቤን በታክስ፣ ግብር ወዘተ ግጣ ግዙፍ ሬቬኑ በመሰብሰብ ለከተማ ዉበትና ስብከት ባጀት ታዘገጃለች ። ሕዝቡም በሚታይ መሻሻል እንዲደግፍ ይደረጋል፣ የፒፒ መራጭ ይሆናል ማለት ነው ።
ፖለቲካ ሁሉ ስለስልጣን፣ ስለገንዘብ፣ ስለዝና እና ስለእምነት ነው ። የዛሬ ድራማ በቀጥታ ስለ ገንዘብና በምርጫው ዙሪያ ስላለው የስልጣን ጉዳይ ነው ። በቃ!