Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
EthioRedSea
Member
Posts: 4089
Joined: 31 Aug 2019, 11:55

ቡሩንዲ ውስጥ መራጮች አዲስ ፕሬዝደንት ለመምረጥ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየጎረፉ ነው።(BBC)

Post by EthioRedSea » 20 May 2020, 11:03

ቡሩንዲ ውስጥ መራጮች አዲስ ፕሬዝደንት ለመምረጥ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየጎረፉ ነው። ገዥው ፕሬዝደንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ ከ15 ዓመታት ሥልጣን በኋላ መንበራቸውን ይለቃሉ። ነገር ግን ከሥልጣን በኋላ የሚኖራቸው ጊዜ በመንግሥት ቤት ነው የሚኖሩት፣ የዕድሜ ዘመን ደሞዝ ይኖራቸዋል፤ ኦፌሴላዊ ሥልጣን እንደሚሰጣቸው ይጠበቃል። ሰባት ዕጩዎች የንኩሩንዚዛዘን መንበር የራሳቸው አድርገው የቡሩንዲ ፕሬዝደንት ለመሆን ይፋለማሉ። በተሻሻለው ሕገ-መንግሥት መሠረት አዲሱ ፕሬዝደንት ለሰባት ዓመታት ያገለግላል፤ ሥልጣን ማራዘም የሚችለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
https://bbc.in/3e47hcB