አንድ የድርድሩ ተሳታፊ እንደሚሉት ከቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት በኋላ ኢትዮጵያ እንዲህ ያለ ዲፕሎማሲያዊ ፈተና ገጥሟት አያውቅም። የዚህ ድርድር ውጤት የአሜሪካና የኢትዮጵያን ግንኙነት ሊያናጋ የሚችል ነው።
“አሁን የምንደራደረው ግብፅን ለማሳመን ሳይሆን አሜሪካንን ላለማስከፋት ነው” ባለሙያው ያሰምሩበታል።
Please wait, video is loading...
አንድ የድርድሩ ተሳታፊ እንደሚሉት ከቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት በኋላ ኢትዮጵያ እንዲህ ያለ ዲፕሎማሲያዊ ፈተና ገጥሟት አያውቅም። የዚህ ድርድር ውጤት የአሜሪካና የኢትዮጵያን ግንኙነት ሊያናጋ የሚችል ነው።
“አሁን የምንደራደረው ግብፅን ለማሳመን ሳይሆን አሜሪካንን ላለማስከፋት ነው” ባለሙያው ያሰምሩበታል።
የህግ ሰነዶች በዚህ ጉድለት ላይ እያሉ ኢትዮጵያ ሶስተኛ ወገን አደራዳሪ ከግብጽ ጋር ሆኖ ያዘጋጀው ሰነድ ላይ እንድትፈርም ጫና መደረጉ አለማቀፍ ህግን የጣሰ ነበር ይላሉ ስለድርድሩ በቅርበት የሚያውቁ ምንጮቻችን። ሆኖም በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በኩል ድርድሩን በስምምነት የመጨረስ ፍላጎት የነበረ ቢሆንም በዋሽንግተን ሲሳተፉ ከነበሩ የህግና የቴክኒክ ጉዳይ ሙያተኞች መካከል አራት ቁልፍ ተደራዳሪዎች ቀድመው ድርድሩን አቋርጠው ወጥተዋል። እንደገና ለሙያዊ እርዳታ ቢፈለጉም የድርድር ሂደቱ ተገቢ አልነበረም ብለው በማመናቸው ፍቃደኛ አልሆኑም።