Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

በትግራይ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አሳሳቢ እየሆኑ መምጣታቸውን የታላቅዋ ትግራይ ብሄራዊ ሸንጎ ገለፀ

Post by Za-Ilmaknun » 07 Feb 2020, 11:26

ባለፈው ዓመት ተመስርቶ በትግራይ በመንቀሳቀስ ላይ ያለው የታላቅዋ ትግራይ ብሔራዊ ሸንጎ (ባይቶና) ተብሎ የሚታወቀው ፓርቲ በክልሉ እየታዩ ናቸው ያላቸው ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አሳሳቢ እየሆኑ መምጣታቸው ገልጿል፡፡ባይቶና በተጨማሪም የመንግስትና ፓርቲ መደበላለቅ፣ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች እየታየ ነው የተባለ የፀጥታና ድህንነት ችግር፣ የክልሉ መገናኛ ብዙሐን ወገንተኝነት፣ በመንግስትና ግል ወገኖች እየታየ ነው የተባለ የሀብት ብክነት የትግራይ ወቅታዊ ፈተናዎች ሲል ተቃዋሚው የፓለቲካ ድርጅት አስቀምጧቸዋል፡፡

https://mereja.com/amharic/v2/215075